የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>የነዳጅ ምርት በመደበቅ በከተማዋ ሰው ሰራሽ እጥረት በሚፈጥሩ አካላት ላይ የሚወሰደው እርምጃ ይቀጥላል- ቢሮው</p>

Jan 15, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 6/2017(ኢዜአ)፦ በከተማዋ የነዳጅ ምርት በመደበቅና በሌሎች ሕገ ወጥ እንቅስቃሴ ተሰማርተው ሰው ሰራሽ የነዳጅ እጥረት በሚፈጥሩ አካላት ላይ የሚወሰደው ጥብቅ እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ገለፀ።

የቢሮ ሃላፊ ወይዘሮ ሀቢባ ሲራጅ የነዳጅ ስርጭትና ቁጥጥርን አስመልክቶ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ የማይክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ በነዳጅ ስርጭት ላይ ልዩ የክትትልና ድጋፍ ስርዓት በመዘርጋት በመዲናዋ የአቅርቦት እጥረት እንዳይፈጠር ጥረት መደረጉን ገልጸዋል።

በዚህም ባለፉት ስድስት ወራት በአማካይ በቀን 3 ነጥብ 45 ሚሊየን ሊትር ነዳጅ ለማደያዎች ሲቀርብ መቆየቱን ገልጸዋል።

ከዚህም ውስጥ በቀን በአማካይ 2 ሚሊየን ሊትር ናፍጣ እና 1 ነጥብ 45 ሚሊዮን ሊትር ቤንዚን መቅረቡን ጠቁመዋል።

በነዳጅ ማደያዎች ላይ በተደረገው የቁጥጥርና ክትትል ሂደት በሕገ-ወጥ ተግባር ውስጥ የገቡ ነዳጅ ማደያዎች ላይ እርምጃ ተወስዷል ብለዋል።

ለአብነትም በሕገ-ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የተገኘ 18 ሺህ 985 ሊትር ቤንዚን እና 9 ሺህ ሊትር ናፍጣ መወረሱን ገልፀዋል።

በአጠቃላይ በሕገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር ከተገኘ 47 ሺ 608 ሊትር ነዳጅ ከ2 ሚሊየን 600 ሺ ብር በላይ በመሸጥ ለመንግስት ገቢ ተደርጓል ብለዋል።

የነዳጅ ምርት በመደበቅ በከተማዋ ሰው ሰራሽ እጥረት በሚፈጥሩ፣ በቴሌ ብር በማይሸጡና ሀያ አራት ሰዓት በማይሰሩ የነዳጅ ማደያዎች ላይ የሚወሰደው እርምጃ በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.