
አዲስ አበባ፤ ጥር 6/2017(ኢዜአ)፦ በከተማዋ የነዳጅ ምርት በመደበቅና በሌሎች ሕገ ወጥ እንቅስቃሴ ተሰማርተው ሰው ሰራሽ የነዳጅ እጥረት በሚፈጥሩ አካላት ላይ የሚወሰደው ጥብቅ እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ገለፀ።
የቢሮ ሃላፊ ወይዘሮ ሀቢባ ሲራጅ የነዳጅ ስርጭትና ቁጥጥርን አስመልክቶ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ የማይክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ በነዳጅ ስርጭት ላይ ልዩ የክትትልና ድጋፍ ስርዓት በመዘርጋት በመዲናዋ የአቅርቦት እጥረት እንዳይፈጠር ጥረት መደረጉን ገልጸዋል።
በዚህም ባለፉት ስድስት ወራት በአማካይ በቀን 3 ነጥብ 45 ሚሊየን ሊትር ነዳጅ ለማደያዎች ሲቀርብ መቆየቱን ገልጸዋል።
ከዚህም ውስጥ በቀን በአማካይ 2 ሚሊየን ሊትር ናፍጣ እና 1 ነጥብ 45 ሚሊዮን ሊትር ቤንዚን መቅረቡን ጠቁመዋል።
በነዳጅ ማደያዎች ላይ በተደረገው የቁጥጥርና ክትትል ሂደት በሕገ-ወጥ ተግባር ውስጥ የገቡ ነዳጅ ማደያዎች ላይ እርምጃ ተወስዷል ብለዋል።
ለአብነትም በሕገ-ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የተገኘ 18 ሺህ 985 ሊትር ቤንዚን እና 9 ሺህ ሊትር ናፍጣ መወረሱን ገልፀዋል።
በአጠቃላይ በሕገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር ከተገኘ 47 ሺ 608 ሊትር ነዳጅ ከ2 ሚሊየን 600 ሺ ብር በላይ በመሸጥ ለመንግስት ገቢ ተደርጓል ብለዋል።
የነዳጅ ምርት በመደበቅ በከተማዋ ሰው ሰራሽ እጥረት በሚፈጥሩ፣ በቴሌ ብር በማይሸጡና ሀያ አራት ሰዓት በማይሰሩ የነዳጅ ማደያዎች ላይ የሚወሰደው እርምጃ በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026