የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ በባህር ዳር ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ።    </p>

Jan 18, 2025

IDOPRESS

ባህር ዳር ጥር 9/2017 (ኢዜአ) ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ የባህር ዳር ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ።

የአማራ ክልል የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ምክር ቤት ጽህፈት ቤት በበኩሉ ህብረተሰቡ ለግድቡ ግንባታ በቦንድ ግዥና በድጋፍ መልክ ይበልጥ እንዲሳተፍ እየተሰራ መሆኑን አስታውቋል ።

ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ለሶስት ጊዜ የወር ደመወዛቸው ቦንድ በመግዛት አሻራቸውን ካሳረፉ የክልሉ የመንግስት ሰራተኞች መካከል አቶ ሞላ አሞኘ አንዱ ናቸው።

የህዳሴ ግድቡ ግንባታ በደረሰበት ደረጃ በመደሰታቸው በቀጣይም ግድቡ ለፍፃሜ እስኪበቃ አቅማቸው በሚፈቅደው ልክ ቦንድ ለመግዛት ማቀዳቸውን ገልጸዋል።

"ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያዊያን የጋራ ምልክት ነው "ያሉት ደግሞ የባህር ዳር ከተማ ነዋሪ አቶ ሞላልኝ አበጀ ናቸው።

ሰርተው ከሚያገኙት ገቢ ቀደም ሲል ለሁለት ጊዜ ያህል የ3 ሺህ 500 ብር ቦንድ በመግዛት ለግድቡ ግንባታ ድጋፍ ማድረጋቸውን ተናግረዋል ።

የክልሉ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ምክር ቤት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አባይነህ ጌጡ በበኩላቸው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታን ለማጠናቀቅ በሚደረገው ጥረት ህብረተሰቡ ድጋፉን በበለጠ እንዲያጠናክር እየተደረገ ይገኛል።

"የክልሉ ህዝብ ግድቡ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ እስካሁን በቦንድ ግዥና በልገሳ አስተዋፅኦ እያደረገ ይገኛል" ብለዋል።

በክልሉ ህብረተሰቡ የግድቡ የመሰረት ድንጋይ ከተጣለበት ጊዜ ጀምሮ በቦንድ ግዥ፣ በልገሳና በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራ ከ39 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመት አስተዋፅኦ ማድረጉን አስታውቀዋል ።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የ25 ዓመት የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ እና ማሻሻያ ማስተር ፕላን ጥናት ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ፣ሐምሌ 20/2018 (ኢዜአ):-የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እስከ ፈረንጆቹ 2049 ድረስ የሚተገበር የ25 ዓመታት ሀገር አቀፍ የኤሌክትሪክ ማስ...

Jul 28, 2026

የኢትዮጵያ የመንገድ መሰረተ ልማቶች የሕዝብን የኢኮኖሚ ትስስር በማሳለጥ የብልፅግና ድልድይ እየገነቡ ነው

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 16/2018 (ኢዜአ) ፦የኢትዮጵያ መንገድ መሰረተ ልማቶች የሕዝብን የኢኮኖሚ ትስስር በማሳለጥ የብልፅግና ድልድይ እየገነቡ መሆኑን የከተማ...

Jul 24, 2026

በጅማ ዞን የሩዝ ምርታማነት እያደገ መጥቷል

ጅማ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ በጅማ ዞን የሩዝ ሰብልን ለማስፋፋት በተከናወነው ሥራ ምርታማነቱ እያደገ መምጣቱን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ገልጿል። በዞኑ...

Jul 22, 2026

በሰሜን ሸዋ ዞን ከ199 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የጠጠር መንገዶች ተገንብተዋል

ደብረ ብርሃን ፤ ሐምሌ 10/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በ199 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ 72 ኪሎ ሜትር የጠ...

Jul 18, 2026