
አዲስ አበባ፤ ጥር 9/2017(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ መጀመር በሀገሪቱ የረዥም ጊዜ ኢንቨስትመንትን ለማስፋፋትና ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ ሰፊ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው የፖሊሲ ጥናት ኢኒስቲትዩት ገለፀ።
በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጥር 2 ቀን 2017 ዓ.ም በይፋ አስጀምረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገበያው በሀገሪቱ የኢኮኖሚ እና የፋይናንስ ምህዳር ውስጥ ታሪካዊ እንደሆነ ጠቁመው፤ ባለሃብቶች ሙዓለ ንዋያቸውን በማፍሰስ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ነው ጥሪ ያቀረቡት።
የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት የማክሮ ፖሊሲ ክፍል አስተባባሪ ተወልደ ግርማ(ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ መጀመር በየደረጃው ዜጎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው።

ገበያው ማሕበረሰቡ ባለው ሃብት ልክ ኢንቨስትመንት ላይ እንዲሳተፍና አቅሙን እንዲጠቀም ከማድረግ አንፃር ሰፊ አስተዋጽኦ የሚያበረክት መሆኑን ነው የተናገሩት።
ከገንዘብ በተጨማሪም የንግድ ሃሳብ ያላቸው ዜጎች በገበያው ውስጥ በመሳተፍ ሃብት ሊያፈሩ የሚችሉበት እድል እንደሚኖር በመጠቆም።
የካፒታል ገበያው ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት አንፃር ዘግይቶ ቢጀመርም ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ባንኮች ጠንካራ በመሆናቸው የተሻሉ ስራዎችን መስራት የሚያስችል ሰፊ እድል መኖሩን ነው የጠቀሱት።
በተለይም የሌሎችን ልምድ በመቀመር ዘርፉን በፍጥነት ማሳደግ የሚያስችል በርካታ መንገዶች እንዳሉም ነው የሚናገሩት።
መንግስት በአሁኑ ወቅት በፋይናንስ ዘርፉ ላይ ተግባራዊ እያደረገ ያለው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጠናክሮ በመቀጠል የካፒታል ገበያውን ማስፋፋት እንደሚችል ነው የጠቀሱት።
የካፒታል ገበያው በተለይ ለግል ባለሃብቱ የረዥም ጊዜ ብድር ከማስገኝት ባለፈ ኢትዮጵያ ላለመችው የዲጂታል ኢኮኖሚ ስኬታማነት ጉልህ ሚና እንደሚያበረክትም ገልጸዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026