የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ መጀመር ኢንቨስትመንትን ለማስፋፋትና ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ ሰፊ አስተዋጽኦ ያበረክታል - የፖሊሲ ጥናት ኢኒስቲትዩት</p>

Jan 18, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 9/2017(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ መጀመር በሀገሪቱ የረዥም ጊዜ ኢንቨስትመንትን ለማስፋፋትና ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ ሰፊ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው የፖሊሲ ጥናት ኢኒስቲትዩት ገለፀ።

በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጥር 2 ቀን 2017 ዓ.ም በይፋ አስጀምረዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገበያው በሀገሪቱ የኢኮኖሚ እና የፋይናንስ ምህዳር ውስጥ ታሪካዊ እንደሆነ ጠቁመው፤ ባለሃብቶች ሙዓለ ንዋያቸውን በማፍሰስ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ነው ጥሪ ያቀረቡት።

የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት የማክሮ ፖሊሲ ክፍል አስተባባሪ ተወልደ ግርማ(ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ መጀመር በየደረጃው ዜጎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው።


ገበያው ማሕበረሰቡ ባለው ሃብት ልክ ኢንቨስትመንት ላይ እንዲሳተፍና አቅሙን እንዲጠቀም ከማድረግ አንፃር ሰፊ አስተዋጽኦ የሚያበረክት መሆኑን ነው የተናገሩት።

ከገንዘብ በተጨማሪም የንግድ ሃሳብ ያላቸው ዜጎች በገበያው ውስጥ በመሳተፍ ሃብት ሊያፈሩ የሚችሉበት እድል እንደሚኖር በመጠቆም።

የካፒታል ገበያው ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት አንፃር ዘግይቶ ቢጀመርም ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ባንኮች ጠንካራ በመሆናቸው የተሻሉ ስራዎችን መስራት የሚያስችል ሰፊ እድል መኖሩን ነው የጠቀሱት።

በተለይም የሌሎችን ልምድ በመቀመር ዘርፉን በፍጥነት ማሳደግ የሚያስችል በርካታ መንገዶች እንዳሉም ነው የሚናገሩት።

መንግስት በአሁኑ ወቅት በፋይናንስ ዘርፉ ላይ ተግባራዊ እያደረገ ያለው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጠናክሮ በመቀጠል የካፒታል ገበያውን ማስፋፋት እንደሚችል ነው የጠቀሱት።

የካፒታል ገበያው በተለይ ለግል ባለሃብቱ የረዥም ጊዜ ብድር ከማስገኝት ባለፈ ኢትዮጵያ ላለመችው የዲጂታል ኢኮኖሚ ስኬታማነት ጉልህ ሚና እንደሚያበረክትም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026