
አዲስ አበባ፤ ጥር 9/2017(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ መጀመር በሀገሪቱ የረዥም ጊዜ ኢንቨስትመንትን ለማስፋፋትና ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ ሰፊ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው የፖሊሲ ጥናት ኢኒስቲትዩት ገለፀ።
በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጥር 2 ቀን 2017 ዓ.ም በይፋ አስጀምረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገበያው በሀገሪቱ የኢኮኖሚ እና የፋይናንስ ምህዳር ውስጥ ታሪካዊ እንደሆነ ጠቁመው፤ ባለሃብቶች ሙዓለ ንዋያቸውን በማፍሰስ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ነው ጥሪ ያቀረቡት።
የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት የማክሮ ፖሊሲ ክፍል አስተባባሪ ተወልደ ግርማ(ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ መጀመር በየደረጃው ዜጎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው።

ገበያው ማሕበረሰቡ ባለው ሃብት ልክ ኢንቨስትመንት ላይ እንዲሳተፍና አቅሙን እንዲጠቀም ከማድረግ አንፃር ሰፊ አስተዋጽኦ የሚያበረክት መሆኑን ነው የተናገሩት።
ከገንዘብ በተጨማሪም የንግድ ሃሳብ ያላቸው ዜጎች በገበያው ውስጥ በመሳተፍ ሃብት ሊያፈሩ የሚችሉበት እድል እንደሚኖር በመጠቆም።
የካፒታል ገበያው ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት አንፃር ዘግይቶ ቢጀመርም ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ባንኮች ጠንካራ በመሆናቸው የተሻሉ ስራዎችን መስራት የሚያስችል ሰፊ እድል መኖሩን ነው የጠቀሱት።
በተለይም የሌሎችን ልምድ በመቀመር ዘርፉን በፍጥነት ማሳደግ የሚያስችል በርካታ መንገዶች እንዳሉም ነው የሚናገሩት።
መንግስት በአሁኑ ወቅት በፋይናንስ ዘርፉ ላይ ተግባራዊ እያደረገ ያለው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጠናክሮ በመቀጠል የካፒታል ገበያውን ማስፋፋት እንደሚችል ነው የጠቀሱት።
የካፒታል ገበያው በተለይ ለግል ባለሃብቱ የረዥም ጊዜ ብድር ከማስገኝት ባለፈ ኢትዮጵያ ላለመችው የዲጂታል ኢኮኖሚ ስኬታማነት ጉልህ ሚና እንደሚያበረክትም ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፣ሐምሌ 20/2018 (ኢዜአ):-የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እስከ ፈረንጆቹ 2049 ድረስ የሚተገበር የ25 ዓመታት ሀገር አቀፍ የኤሌክትሪክ ማስ...
Jul 28, 2026
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 16/2018 (ኢዜአ) ፦የኢትዮጵያ መንገድ መሰረተ ልማቶች የሕዝብን የኢኮኖሚ ትስስር በማሳለጥ የብልፅግና ድልድይ እየገነቡ መሆኑን የከተማ...
Jul 24, 2026
ጅማ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ በጅማ ዞን የሩዝ ሰብልን ለማስፋፋት በተከናወነው ሥራ ምርታማነቱ እያደገ መምጣቱን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ገልጿል። በዞኑ...
Jul 22, 2026
ደብረ ብርሃን ፤ ሐምሌ 10/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በ199 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ 72 ኪሎ ሜትር የጠ...
Jul 18, 2026