አዲስ አበባ፤ ጥር 9/2017(ኢዜአ)፦ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በኢትዮጵያውያን ተጀምሮ በኢትዮጵያውያን የሚጠናቀቅ የኩራት ምንጭ ነው ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ኃላፊ ገብረመስቀል ጫላ ገለጹ።
የክልሉ ሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች ለህዳሴ ግድብ ግንባታ ከ122 ሺህ ብር በላይ የቦንድ ግዢ ፈጽመዋል።
የቦንድ ግዢው የኢትዮጵያ ልማት ባንክ አርባምንጭ ዲስትሪክት ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘሪሁን በቀለ በተገኙበት ተከናውኗል።
አቶ ገብረመስቀል ጫላ በዚሁ ወቅት እንዳሉት የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በኢትዮጵያውያን ተጀምሮ በኢትዮጵያውያን የሚጠናቀቅ የኩራታችን ምንጭ ነው።
የግድቡ ግንባታ እስኪጠናቀቅ ድረስ ሁሉም የበኩሉን ድርሻ መወጣቱን እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች ለግድቡ ግንባታ ቦንድ በመግዛት አሻራቸውን በማስቀመጣቸው መደሰታቸውን ገልጸዋል።
የግድቡ ግንባታ እስኪጠናቀቅም የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ መግለጻቸውን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ ፤የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርት ተገልጋዮች ፋይዳ መታወቂያን ተጠቅመው በዲጂታል አማራጭ ትኬት የሚቆርጡበት አሰራር ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 03/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የለማ የትራንስፖርት ኦፕሬተሮችንና የጭነት ባለቤቶችን የሚገናኝ መተግበሪያ አስጀምሯል። ...
Feb 12, 2025