
አዲስ አበባ፤ ጥር 9/2017(ኢዜአ)፦ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በኢትዮጵያውያን ተጀምሮ በኢትዮጵያውያን የሚጠናቀቅ የኩራት ምንጭ ነው ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ኃላፊ ገብረመስቀል ጫላ ገለጹ።
የክልሉ ሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች ለህዳሴ ግድብ ግንባታ ከ122 ሺህ ብር በላይ የቦንድ ግዢ ፈጽመዋል።
የቦንድ ግዢው የኢትዮጵያ ልማት ባንክ አርባምንጭ ዲስትሪክት ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘሪሁን በቀለ በተገኙበት ተከናውኗል።
አቶ ገብረመስቀል ጫላ በዚሁ ወቅት እንዳሉት የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በኢትዮጵያውያን ተጀምሮ በኢትዮጵያውያን የሚጠናቀቅ የኩራታችን ምንጭ ነው።

የግድቡ ግንባታ እስኪጠናቀቅ ድረስ ሁሉም የበኩሉን ድርሻ መወጣቱን እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች ለግድቡ ግንባታ ቦንድ በመግዛት አሻራቸውን በማስቀመጣቸው መደሰታቸውን ገልጸዋል።
የግድቡ ግንባታ እስኪጠናቀቅም የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ መግለጻቸውን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026