
አዲስ አበባ፤ ጥር 9/2017(ኢዜአ)፦ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በኢትዮጵያውያን ተጀምሮ በኢትዮጵያውያን የሚጠናቀቅ የኩራት ምንጭ ነው ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ኃላፊ ገብረመስቀል ጫላ ገለጹ።
የክልሉ ሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች ለህዳሴ ግድብ ግንባታ ከ122 ሺህ ብር በላይ የቦንድ ግዢ ፈጽመዋል።
የቦንድ ግዢው የኢትዮጵያ ልማት ባንክ አርባምንጭ ዲስትሪክት ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘሪሁን በቀለ በተገኙበት ተከናውኗል።
አቶ ገብረመስቀል ጫላ በዚሁ ወቅት እንዳሉት የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በኢትዮጵያውያን ተጀምሮ በኢትዮጵያውያን የሚጠናቀቅ የኩራታችን ምንጭ ነው።

የግድቡ ግንባታ እስኪጠናቀቅ ድረስ ሁሉም የበኩሉን ድርሻ መወጣቱን እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች ለግድቡ ግንባታ ቦንድ በመግዛት አሻራቸውን በማስቀመጣቸው መደሰታቸውን ገልጸዋል።
የግድቡ ግንባታ እስኪጠናቀቅም የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ መግለጻቸውን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026