
አዲስ አበባ፤ ጥር 9/2017(ኢዜአ)፦ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በኢትዮጵያውያን ተጀምሮ በኢትዮጵያውያን የሚጠናቀቅ የኩራት ምንጭ ነው ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ኃላፊ ገብረመስቀል ጫላ ገለጹ።
የክልሉ ሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች ለህዳሴ ግድብ ግንባታ ከ122 ሺህ ብር በላይ የቦንድ ግዢ ፈጽመዋል።
የቦንድ ግዢው የኢትዮጵያ ልማት ባንክ አርባምንጭ ዲስትሪክት ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘሪሁን በቀለ በተገኙበት ተከናውኗል።
አቶ ገብረመስቀል ጫላ በዚሁ ወቅት እንዳሉት የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በኢትዮጵያውያን ተጀምሮ በኢትዮጵያውያን የሚጠናቀቅ የኩራታችን ምንጭ ነው።

የግድቡ ግንባታ እስኪጠናቀቅ ድረስ ሁሉም የበኩሉን ድርሻ መወጣቱን እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች ለግድቡ ግንባታ ቦንድ በመግዛት አሻራቸውን በማስቀመጣቸው መደሰታቸውን ገልጸዋል።
የግድቡ ግንባታ እስኪጠናቀቅም የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ መግለጻቸውን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፣ሐምሌ 20/2018 (ኢዜአ):-የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እስከ ፈረንጆቹ 2049 ድረስ የሚተገበር የ25 ዓመታት ሀገር አቀፍ የኤሌክትሪክ ማስ...
Jul 28, 2026
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 16/2018 (ኢዜአ) ፦የኢትዮጵያ መንገድ መሰረተ ልማቶች የሕዝብን የኢኮኖሚ ትስስር በማሳለጥ የብልፅግና ድልድይ እየገነቡ መሆኑን የከተማ...
Jul 24, 2026
ጅማ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ በጅማ ዞን የሩዝ ሰብልን ለማስፋፋት በተከናወነው ሥራ ምርታማነቱ እያደገ መምጣቱን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ገልጿል። በዞኑ...
Jul 22, 2026
ደብረ ብርሃን ፤ ሐምሌ 10/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በ199 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ 72 ኪሎ ሜትር የጠ...
Jul 18, 2026