
ሐረር፤ ጥር 13/2017(ኢዜአ)፡- በሐረሪ ክልል እየተከናወነ የሚገኘው የመስኖ ልማት የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነትን ከማጎልበት ባለፈ ገበያን እያረጋጋ እንደሚገኝ ተገልጿል።
በመስኖ ልማቱ የተሻለ ምርት እያገኙ መሆኑን አርሶ አደሮች ተናግረዋል።
የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ልማት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሮዛ ዑመር እንደገለጹት፤ በክልሉ በዘንድሮው በጋ ወራት 4ሺህ 700 ሄክታር መሬት ልዩ ልዩ አትክልትና ፍራፍሬ በመስኖ እየለማ ነው።

በዓመት ሶስት ጊዜ ለማምረት በሚከናወነው የመስኖ ልማት የመጀመሪያ ዙር የምርት መሰብሰብ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝም ጠቅሰዋል።
በዚህም አርሶ አደሩ አስፈላጊው የምርት ግብዓት ቀርቦለት ምርትና ምርታማነትን የማጎልበት ስራ በተጠናከረ መልኩ እያከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በተለይ አርሶ አደሩ ያመረተውን ምርት በቀጥታ ለከተማው ማህበረሰብ በማቅረብ የዋጋ ማረጋጋት ስራ እየተከናወነ ነው ብለዋል።
ለልማት ሰራተኞችና ለአርሶ አደሮች ስልጠና በመስጠት የምርት ግብዓት በማሟላት የመስኖ ልማቱ በተያዘው እቅድ እየተከናወነ ይገኛል ያሉት ደግሞ በክልሉ የሶፊ ወረዳ ግብርና ልማት አስተባባሪ አቶ ጃፈር ከዲር ናቸው።
በወረዳው የሚከናወነው የግብርና ልማት ስራ ተረጂነትን ለመቀነስ እያገዘ መሆኑን ጠቁመው፤ በተለይ ከመስኖ ልማቱ 200 ሺህ ኩንታል ምርት ለማግኘት መታቀዱን ገልጸዋል።

ዘንድሮ ለመስኖ የሚያስፈልጉ ሁሉም አቅርቦቶች በተሻለ መልኩ በመከናወናቸው እና የግብርና ባለሙያዎች እገዛ ከፍተኛ በመሆኑ የተሻለ ምርት ማምረት ችያለሁ ያሉት ደግሞ በክልሉ ሶፊ ወረዳ አርሶ አደር መጂድ አብዱላሂ ናቸው።
ወጣት አርሶ አደር ሙራድ መጂድ በበኩሉ ቀደም ሲል በቆሎ እናመርት ነበር፤ በመስኖ ሽንኩርት ማልማት እንደምንችል የግብርና ባለሙያዎች በመከሩን መሰረት አምና ካመረትነው የሽንኩርት ልማት 2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር ገቢ ማግኘት ችለናል ብሏል።

ዘንድሮም ከ400 ኩንታል በላይ ምርት ለማምረት በትጋት እየሰሩ እንደሚገኙም አርሶ አደሩ ገልጿል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026