የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

<p>ለ2017/18 የምርት ዘመን የተገዛ የአፈር ማዳበሪያ ወደ ትግራይ ክልል እየተጓጓዘ ነው</p>

Jan 21, 2025

IDOPRESS

መቀሌ፤ ጥር 13/2017(ኢዜአ)፡- ለ2017/18 የምርት ዘመን የተገዛ የአፈር ማዳበሪያ ወደ ትግራይ ክልል እየተጓጓዘ መሆኑን በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የእርሻና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ አበራ ከደነው ለኢዜአ እንደገለፁት፤ ለቀጣይ የምርት ዘመን ለክልሉ አንድ ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ያስፈልጋል።

የፌዴራል መንግስት በግብርና ሚኒስቴር በኩል ከፍተኛ ክትትልና ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ገልጸው፤ በቀጣይ የምርት ዘመን የግብርና ግብዓት እጥረት ያጋጥማል የሚል ስጋት እንደሌለ ጠቁመዋል።

በፌዴራል መንግስት ለቀጣይ የምርት ዘመን የሚሆን የተገዛ የአፈር ማዳበሪያ ወደ ክልሉ ብሎም መጋዘን ወደ ተዘጋጀላቸው ወረዳዎች መጓጓዝ መጀመሩን ተናግረዋል።

ግብዓቱ ወደ ክልሉ በወቅቱ መግባት መጀመሩ ምርትና ምርታማነት መጨመር ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልጸዋል።

የክልሉ የአፈር ማዳበሪያ ፍላጎት እየጨመረ መምጣቱን እና የፌዴራል መንግስትም የሚያስፈልገውን ማዳበሪያ እያቀረበ መሆኑን አመልክተዋል።


የምርጥ ዘር አቅርቦት እጥረት እንዳያጋጥም ከሞዴል አርሶ አደሮች የህብረት ስራ ማህበራትና የምርምር ተቋማት ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑንም ጨምረው ተናግረዋል።

በክልሉ 2016/17 የምርት ዘመን የእርሻ ግብዓቶች በተለይ የአፈር ማዳበሪያ በወቅቱ ለአርሶ አደሩ እንዲከፋፈል መደረጉ ለተገኘው የ13 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ከፍተኛ ሚና እንደነበረውም አቶ አበራ አውስተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.