
መቀሌ፤ ጥር 13/2017(ኢዜአ)፡- ለ2017/18 የምርት ዘመን የተገዛ የአፈር ማዳበሪያ ወደ ትግራይ ክልል እየተጓጓዘ መሆኑን በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የእርሻና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ አበራ ከደነው ለኢዜአ እንደገለፁት፤ ለቀጣይ የምርት ዘመን ለክልሉ አንድ ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ያስፈልጋል።
የፌዴራል መንግስት በግብርና ሚኒስቴር በኩል ከፍተኛ ክትትልና ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ገልጸው፤ በቀጣይ የምርት ዘመን የግብርና ግብዓት እጥረት ያጋጥማል የሚል ስጋት እንደሌለ ጠቁመዋል።
በፌዴራል መንግስት ለቀጣይ የምርት ዘመን የሚሆን የተገዛ የአፈር ማዳበሪያ ወደ ክልሉ ብሎም መጋዘን ወደ ተዘጋጀላቸው ወረዳዎች መጓጓዝ መጀመሩን ተናግረዋል።
ግብዓቱ ወደ ክልሉ በወቅቱ መግባት መጀመሩ ምርትና ምርታማነት መጨመር ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልጸዋል።
የክልሉ የአፈር ማዳበሪያ ፍላጎት እየጨመረ መምጣቱን እና የፌዴራል መንግስትም የሚያስፈልገውን ማዳበሪያ እያቀረበ መሆኑን አመልክተዋል።

የምርጥ ዘር አቅርቦት እጥረት እንዳያጋጥም ከሞዴል አርሶ አደሮች የህብረት ስራ ማህበራትና የምርምር ተቋማት ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑንም ጨምረው ተናግረዋል።
በክልሉ 2016/17 የምርት ዘመን የእርሻ ግብዓቶች በተለይ የአፈር ማዳበሪያ በወቅቱ ለአርሶ አደሩ እንዲከፋፈል መደረጉ ለተገኘው የ13 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ከፍተኛ ሚና እንደነበረውም አቶ አበራ አውስተዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026