
አዲስ አበባ፤ ጥር 13/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ በቴሌኮም መሰረተ ልማት ተደራሽነት እመርታዊ ለውጥ እያስመዘገበች እንደምትገኝ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) ገለጹ።
ሚኒስትሩ ይህን ያሉት በአዲስ አበባ እየተካሄደ በሚገኘው የኢንተርኔት ልማት ጉባኤ መክፈቻ መርሐ ግብር ላይ ነው።
ኢንተርኔት ለኢኮኖሚ ዕድገት፣ ለማህበራዊ ትስስርና ልማት ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት ጠቁመው፥ ለቀጣናዊ ትብብርና ለፈጠራ ማደግ ምቹ ምህዳር የሚፈጥር ነውም ብለዋል።
ሆኖም በቀጣናው ካለው ፍላጎት አንጻር የኢንተርኔት ተደራሽነት አሁንም ተግዳሮት ሆኖ መቀጠሉን አንስተዋል።
ኢትዮጵያ በዲጂታል 2025 ስትራቴጂ መሰረት የዲጂታል ሽግግርን እውን የሚያደርጉ ተግባራትን እያከናወነች መሆኑን ጠቅሰዋል።

የቴሌኮም መሰረተ ልማትን በከፍተኛ ሁኔታ እያስፋፋችና እያዘመነች መሆኑን ገልጸው የ4ጂ ኔትወርክ ተደራሽነት ሀገራዊ ሽፋን 34 ነጥብ 8 በመቶ መድረሱን አንስተዋል።
5ጂ ኔትወርክም በትላልቅ ከተሞች አገልግሎት መጀመሩንና ይህም የኢንተርኔት ተደራሽነትንና ተጠቃሚነትን ያሳድጋል ነው ያሉት።
ኢትዮ ቴሌኮም የጀመረው ቴሌ ብር ከ51 ሚሊዮን በላይ ተጠቃሚዎችን በማፍራት አካታች የዲጂታል ኢኮኖሚን ለመገንባት ትልቅ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝም ገልጸዋል።
የግል የቴሌኮም ኦፕሬተሮችና የዳታ ማዕከል አቅራቢዎች በሀገሪቱ እንዲሰማሩ በማድረግ ዲጂታል መሰረተ ልማት ግንባታ ላይ አሻራቸውን እያሳረፉ እንደሚገኙ ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያ የጀመረችው የዲጂታል ሽግግር ሁሉንም ዜጎች ተጠቃሚ የሚያደርግ ዘመናዊ አገልግሎትና አካታች ኢኮኖሚን ለመገንባትና በአፍሪካ የዲጂታል አብዮት መሪ እንድትሆን የሚያስችል ነው ብለዋል።
ለሦስት ቀናት የሚቆየው የኢንተርኔት ልማት ጉባኤ በኢትዮጵያ እና በሌሎች የኢጋድ አባል ሀገራት የኢንተርኔት መሠረተ ልማቶችን ይበልጥ ለማሳደግ እንደሚረዳ ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026