የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን እና የጣልያኑ ዋንኮ ኢታሊ የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ</p>

Jan 22, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 12/2017 (ኢዜአ)፦የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ሕንጻዎችን በፍጥነትና በጥራት ለመገንባት የሚያስችል የግንባታ ቴክኖሎጂ ባለቤት የሚያደርገውን ስምምነት ከጣልያኑ ዋንኮ ኢታሊ ኩባንያ ጋር ተፈራርሟል።

ስምምነቱ ኮርፖሬሽኑ የመኖሪያ ቤት አሰራር ስልትን የሚያዘምን ግዙፍ የተገጣጣሚ ቤቶች ፋብሪካ ተከላን ለማከናወን ያስችለዋል።

የግንባታ ቴክኖሎጂው የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የኮንስትራክሽን ዘርፉን ለማዘመን እያደረገ ያለውን ጥረት እንደሚያግዝ ተመላክቷል።

ቴክኖሎጂው በቀን አንድ የሕንጻ ወለል መገንባት የሚያስችል ሲሆን ቪላ ቤትን ጨምሮ ሰማይ ጠቀስ ሕንጻዎች በአጭር ጊዜ መገንባት የሚያስችል መሆኑን የኮርፖሬሽኑ መረጃ ያመለክታል።

ኮርፖሬሽኑ ከአልሙኒየም ፎርምወርክ ቴክኖሎጂ ቀጥሎ ለኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ያስተዋወቀው ሁለተኛው ዘመናዊ የግንባታ ቴክኖሎጂ እንደሆነም አስታውቋል።

የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ረሻድ ከማል በፊርማ ሥነ ስርዓቱ ላይ እንደተናገሩት ኮርፖሬሽኑ ጊዜን ፣ፍጥነትን እና ውጤታማ የበጀት አጠቃቀም መርህን በቀላሉ ለመተግበር የሚያስችሉ ዘመናዊ የግንባታ ቴክኖሎጂዎችን ጥቅም ላይ ለማዋል ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ነው።

የጣሊያኑ ዋንኮ ኩባንያ የሚታወቅበትን የተገጣጣሚ ቤቶች ግንባታ ቴክኖሎጂ ወደ ኢትዮጵያ ለማምጣት ተገቢውን ሳይንሳዊ ጥናትና ለዚሁ የሚያስፈልጉ ዝግጅቶችንም ኮርፖሬሽኑ ሲያደርግ መቆየቱን አመልክተዋል።

አስተማማኝ ግብዓት አቅርቦት ለመፍጠር ግዙፍ የግብዓት ማምረቻ ፋብሪካ በመትከል በቅርቡ ማስመረቁን አስታውሰዋል።

መሰል የግንባታ ቴክኖሎጂዎችን በማላማድ የወቅቱ የአገራችን የመኖሪያ ቤት ችግርን ለመፍታት ኮርፖሬሽኑ እያደረገ ያለውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ነው አቶ ረሻድ የገለጹት።

የፋብሪካ ተከላውን በአጭር ጊዜ በማጠናቀቅ ወደ ሥራ ለማስገባት አስፈላጊው ዝግጅት መጠናቀቁን ጠቁመዋል።

የዋንኮ ኢታሊ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ማሲሞ ቡስነሌ በበኩላቸው የግንባታ ቴክኖሎጂውን ወደ ኢትዮጵያ ለማምጣት መንግስታዊውን የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽንን መምረጣቸውን ገልጸዋል።


የፋብሪካ ተከላውን በአጭር ጊዜ ለማከናወን መዘጋጀታቸውን ገልጸው ፣ በፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በኩል እየተደረገ ያለውን ዝግጅት ተዘዋውረው እንደተመለከቱም ጠቁመዋል።

ፋብሪካው በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ገላን አካባቢ በሚገኘው የኮርፖሬሽኑ 10 ሄክታር ይዞታ ላይ እንደሚገነባ ከኮርፖሬሽኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026