የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>ኢትዮ ቴሌኮም 5 ነጥብ 5 ሚሊየን ሰዎችን ለዲጂታል መታወቂያ(ፋይዳ) መዝግቧል</p>

Feb 6, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 21/2017(ኢዜአ)፡-ኢትዮ ቴሌኮም እስካሁን 5 ነጥብ 5 ሚሊየን ሰዎችን ለዲጂታል መታወቂያ(ፋይዳ) መመዝገቡን አስታወቀ።

ከ427 ሺህ በላይ የመታወቂያ ካርዶች ታትመው ለህብረተሰቡ ተደራሽ መሆናቸውንም ገልጿል።

የኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ከስተመር ኤክስፒሪያንስና ኳሊቲ ኦፊሰር ሰለሞን አበራ እንዳሉት ኢትዮ ቴሌኮም ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ እየሰራ ይገኛል፡፡

በዚህም ከብሄራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ጋር ስምምነት በማድረግ በ275 ከተሞች የዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ እየተካሄደ ነው ብለዋል።

በአገር አቀፍ ደረጃ ለዲጂታል መታወቂያ ከተመዘገቡ 11 ነጥብ 5 ሚሊየን ዜጎች ውስጥ ኢትዮ ቴሌኮም 5 ነጥብ 5 ሚሊየኑን መመዝገቡን ተናግረዋል።

በዓመት እስከ 48 ሚሊየን መታወቂያዎችን ማተም የሚችሉ ማሽኖች በማስገባት የህትመት ስራን እያፋጠነ ነው ያሉት አቶ ሰለሞን አበራ፥ መታወቂያው ለ10 ዓመት ማገልገል እንደሚችል ጠቁመዋል፡፡

እስካሁን ባለው ሂደት በአዲስ አበባ፣ በአዳማ፣ ሃዋሳ፣ ነቀምትና ወላይታ ሶዶ ከተሞች መታወቂያ እየታተመ ለህብረተሰቡ ተደራሽ መሆኑን አንስተዋል።

ኢትዮ ቴሌኮም የመታወቂያ ህትመት አገልግሎቱን እስከ የካቲት ወር አጋማሽ ድረስ በሁሉም አካባቢዎች ለማስፋት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

የካርድ ህትመት ከተጀመረ ከሁለት ወር በላይ ያስቆጠረ ሲሆን፥ 427 ሺህ የመታወቂያ ካርዶች ታትመው ለህብረተሰቡ እንዲደርሱ መደረጉንም ነው የገለጹት።

በአዲስ አበባ 63 የካርድ መረከቢያ ቦታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው፥ በቴሌ ብር ክፍያ በመፈፀም የዲጂታል መታወቂያ ካርዱን መውሰድ እንደሚችሉም ተናግረዋል።


በኢትዮ ቴሌኮም የዲጂታል መታወቂያ ካርዳቸውን ለመውሰድ ከመጡ ተገልጋዮች መካከል ጌታቸው ዓለሙ እና ባንቴ ጌትነት በበኩላቸው፥ ከምዝገባ ጀምሮ ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘታቸውን ገልጸዋል።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026