የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>ኢትዮ ቴሌኮም 5 ነጥብ 5 ሚሊየን ሰዎችን ለዲጂታል መታወቂያ(ፋይዳ) መዝግቧል</p>

Feb 6, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 21/2017(ኢዜአ)፡-ኢትዮ ቴሌኮም እስካሁን 5 ነጥብ 5 ሚሊየን ሰዎችን ለዲጂታል መታወቂያ(ፋይዳ) መመዝገቡን አስታወቀ።

ከ427 ሺህ በላይ የመታወቂያ ካርዶች ታትመው ለህብረተሰቡ ተደራሽ መሆናቸውንም ገልጿል።

የኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ከስተመር ኤክስፒሪያንስና ኳሊቲ ኦፊሰር ሰለሞን አበራ እንዳሉት ኢትዮ ቴሌኮም ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ እየሰራ ይገኛል፡፡

በዚህም ከብሄራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ጋር ስምምነት በማድረግ በ275 ከተሞች የዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ እየተካሄደ ነው ብለዋል።

በአገር አቀፍ ደረጃ ለዲጂታል መታወቂያ ከተመዘገቡ 11 ነጥብ 5 ሚሊየን ዜጎች ውስጥ ኢትዮ ቴሌኮም 5 ነጥብ 5 ሚሊየኑን መመዝገቡን ተናግረዋል።

በዓመት እስከ 48 ሚሊየን መታወቂያዎችን ማተም የሚችሉ ማሽኖች በማስገባት የህትመት ስራን እያፋጠነ ነው ያሉት አቶ ሰለሞን አበራ፥ መታወቂያው ለ10 ዓመት ማገልገል እንደሚችል ጠቁመዋል፡፡

እስካሁን ባለው ሂደት በአዲስ አበባ፣ በአዳማ፣ ሃዋሳ፣ ነቀምትና ወላይታ ሶዶ ከተሞች መታወቂያ እየታተመ ለህብረተሰቡ ተደራሽ መሆኑን አንስተዋል።

ኢትዮ ቴሌኮም የመታወቂያ ህትመት አገልግሎቱን እስከ የካቲት ወር አጋማሽ ድረስ በሁሉም አካባቢዎች ለማስፋት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

የካርድ ህትመት ከተጀመረ ከሁለት ወር በላይ ያስቆጠረ ሲሆን፥ 427 ሺህ የመታወቂያ ካርዶች ታትመው ለህብረተሰቡ እንዲደርሱ መደረጉንም ነው የገለጹት።

በአዲስ አበባ 63 የካርድ መረከቢያ ቦታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው፥ በቴሌ ብር ክፍያ በመፈፀም የዲጂታል መታወቂያ ካርዱን መውሰድ እንደሚችሉም ተናግረዋል።


በኢትዮ ቴሌኮም የዲጂታል መታወቂያ ካርዳቸውን ለመውሰድ ከመጡ ተገልጋዮች መካከል ጌታቸው ዓለሙ እና ባንቴ ጌትነት በበኩላቸው፥ ከምዝገባ ጀምሮ ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘታቸውን ገልጸዋል።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026