
ጥር 26/2017(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ወጣቶች የኮደርስ ስልጠና እንዲወስዱ ምቹ ሁኔታዎችን ከማመቻቸት ጎን ለጎን ግንዛቤ ለሚያሳድጉ ተግባራት ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ባለስልጣን ገልጿል።
የክልሉ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የክልሉ የኢትዮ ኮደርስ ቴክኒክ ኮሚቴ ሰብሳቢ ኢንጂነር ጅማ ቱሉ በጉዳዩ ላይ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል።
ኢንጂነር ጅማ ቱሉ በቆይታቸው የክልሉ ወጣቶች ዘመኑ የሚጠይቀውን እውቀት ጨብጠው ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ጊዜና ቦታ ሳይገድባቸው ስልጠናውን መከታተል እንዲችሉ ምቹ ሁኔታዎች መፈጠራቸውን ተናግረዋል።

የአብይ ኮሚቴና የቴክኒክ ኮሚቴዎች ተዋቅረው ከክልል እስከ ዞኖችና ከተሞች ስልጠናውን እያስተባበሩ መሆኑንም አስረድተዋል።
በዚህም በስልጠናው የመንግስት ሰራተኞች፤ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መምህራንና ተማሪዎች፤ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች መምህራንና ተማሪዎች እየተሳተፉ መሆኑን ገልጸዋል።
ስልጠናውን በኦንላይን መከታተል የሚያስችላቸው የመንግስት ተቋማት፤ ትምህርት ቤቶች፤ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆችና የወጣቶች ማዕከላት መዘጋጀታቸውንም ጨምረው ተናግረዋል።

እስካሁን በተሰራው ስራ 141 ሺህ የመንግስት ሰራተኖች፣ 84 ሺህ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች፣ 30 ሺህ የቴክኒክና ሙያ መምህራንና ተማሪዎች የኮደርስ ስልጠና መውሰዳቸውን ገልጸዋል።
እንደ ኢንጂነር ጅማ ገለጻ ዜጎች ስልጠናው በስፋት መውሰድ እንዲችሉ ሚኒ ሚዲያ፤ ማህበራዊ ሚዲያና ሌሎች አማራጮችን በመጠቀም ግንዛቤ የማሳደግ ስራ በትኩረት እየተሰራ ነው።
በክልሉ ዞኖችና ከተሞች ህዝብ የሚበዛባቸውን አካባቢዎች በመለየት ለመርሃ ግብሩ አገልግሎት ብቻ የሚውል ኢንተርኔት መዘጋጀቱንም ጨምረው ጠቅሰዋል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026