የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>በመቀሌ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን እየተገነባ ያለው የውሃ ማስፋፊያ ፕሮጀክት በመጠናቀቅ ላይ ነው</p>

Feb 6, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 28/2017(ኢዜአ)፦በመቀሌ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ከ61 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው የውሃ ማስፋፊያ ፕሮጀክት የግንባታና የመስመር ዝርጋታ ስራዎች በመጠናቀቅ ላይ መሆናቸው ተገልጿል።

የልዩ ኢኮኖሚ ዞኑ ስራ አስኪያጅ አቶ ፍሊሞን ተረፈ እንደገለጹት የፕሮጀክቱ መጠናቀቅ በልዩ ኢኮኖሚ ዞኑ ከዚህ በፊት የነበረውን የውሃ አቅርቦት መጠንና ጥራት ይበልጡን የሚያሻሽል ነው።

በልዩ ኢኮኖሚ ዞኑ ያለውን የውሃ አቅርቦት በከፍተኛ ሁኔታ ለማሻሻል ከመቀሌ ከተማ አስተዳደር ውሃ አገልግሎት ጋር በቅንጅት በመስራት ተጨማሪ የውሃ ጉድጓድ ለመጠቀም የሚያስችል የመሰረተ ልማት ዝርጋታ ስራዎች መጠናቀቃቸውን ስራ አስኪያጁ ጨምረው ገልጸዋል፡፡

አሁን ላይ የውሃ ፕሮጀክቱን የመስመር ዝርጋታ የማጠናቀቅ ስራዎች መከናወናቸውንም ተናግረዋል።

ስራ አስኪያጁ አክለውም የውሃ ፕሮጀክቱ አሁን ላይ ተጨማሪ 20 ሊትር በሰከንድ ማመንጨት የሚችል መሆኑንና ይህም በልዩ ኢኮኖሚ ዞኑ ያለውን የውሃ አቅርቦት ጥራትና ተደራሽነት እንደሚያሻሽለው መግለጻቸውን ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.