
አዲስ አበባ፤ ጥር 28/2017(ኢዜአ)፦በመቀሌ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ከ61 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው የውሃ ማስፋፊያ ፕሮጀክት የግንባታና የመስመር ዝርጋታ ስራዎች በመጠናቀቅ ላይ መሆናቸው ተገልጿል።
የልዩ ኢኮኖሚ ዞኑ ስራ አስኪያጅ አቶ ፍሊሞን ተረፈ እንደገለጹት የፕሮጀክቱ መጠናቀቅ በልዩ ኢኮኖሚ ዞኑ ከዚህ በፊት የነበረውን የውሃ አቅርቦት መጠንና ጥራት ይበልጡን የሚያሻሽል ነው።
በልዩ ኢኮኖሚ ዞኑ ያለውን የውሃ አቅርቦት በከፍተኛ ሁኔታ ለማሻሻል ከመቀሌ ከተማ አስተዳደር ውሃ አገልግሎት ጋር በቅንጅት በመስራት ተጨማሪ የውሃ ጉድጓድ ለመጠቀም የሚያስችል የመሰረተ ልማት ዝርጋታ ስራዎች መጠናቀቃቸውን ስራ አስኪያጁ ጨምረው ገልጸዋል፡፡
አሁን ላይ የውሃ ፕሮጀክቱን የመስመር ዝርጋታ የማጠናቀቅ ስራዎች መከናወናቸውንም ተናግረዋል።
ስራ አስኪያጁ አክለውም የውሃ ፕሮጀክቱ አሁን ላይ ተጨማሪ 20 ሊትር በሰከንድ ማመንጨት የሚችል መሆኑንና ይህም በልዩ ኢኮኖሚ ዞኑ ያለውን የውሃ አቅርቦት ጥራትና ተደራሽነት እንደሚያሻሽለው መግለጻቸውን ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026