
አዲስ አበባ፤ ጥር 28/2017(ኢዜአ)፦በመቀሌ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ከ61 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው የውሃ ማስፋፊያ ፕሮጀክት የግንባታና የመስመር ዝርጋታ ስራዎች በመጠናቀቅ ላይ መሆናቸው ተገልጿል።
የልዩ ኢኮኖሚ ዞኑ ስራ አስኪያጅ አቶ ፍሊሞን ተረፈ እንደገለጹት የፕሮጀክቱ መጠናቀቅ በልዩ ኢኮኖሚ ዞኑ ከዚህ በፊት የነበረውን የውሃ አቅርቦት መጠንና ጥራት ይበልጡን የሚያሻሽል ነው።
በልዩ ኢኮኖሚ ዞኑ ያለውን የውሃ አቅርቦት በከፍተኛ ሁኔታ ለማሻሻል ከመቀሌ ከተማ አስተዳደር ውሃ አገልግሎት ጋር በቅንጅት በመስራት ተጨማሪ የውሃ ጉድጓድ ለመጠቀም የሚያስችል የመሰረተ ልማት ዝርጋታ ስራዎች መጠናቀቃቸውን ስራ አስኪያጁ ጨምረው ገልጸዋል፡፡
አሁን ላይ የውሃ ፕሮጀክቱን የመስመር ዝርጋታ የማጠናቀቅ ስራዎች መከናወናቸውንም ተናግረዋል።
ስራ አስኪያጁ አክለውም የውሃ ፕሮጀክቱ አሁን ላይ ተጨማሪ 20 ሊትር በሰከንድ ማመንጨት የሚችል መሆኑንና ይህም በልዩ ኢኮኖሚ ዞኑ ያለውን የውሃ አቅርቦት ጥራትና ተደራሽነት እንደሚያሻሽለው መግለጻቸውን ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026