
አዲስ አበባ፤ ጥር 28/2017(ኢዜአ)፦በመቀሌ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ከ61 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው የውሃ ማስፋፊያ ፕሮጀክት የግንባታና የመስመር ዝርጋታ ስራዎች በመጠናቀቅ ላይ መሆናቸው ተገልጿል።
የልዩ ኢኮኖሚ ዞኑ ስራ አስኪያጅ አቶ ፍሊሞን ተረፈ እንደገለጹት የፕሮጀክቱ መጠናቀቅ በልዩ ኢኮኖሚ ዞኑ ከዚህ በፊት የነበረውን የውሃ አቅርቦት መጠንና ጥራት ይበልጡን የሚያሻሽል ነው።
በልዩ ኢኮኖሚ ዞኑ ያለውን የውሃ አቅርቦት በከፍተኛ ሁኔታ ለማሻሻል ከመቀሌ ከተማ አስተዳደር ውሃ አገልግሎት ጋር በቅንጅት በመስራት ተጨማሪ የውሃ ጉድጓድ ለመጠቀም የሚያስችል የመሰረተ ልማት ዝርጋታ ስራዎች መጠናቀቃቸውን ስራ አስኪያጁ ጨምረው ገልጸዋል፡፡
አሁን ላይ የውሃ ፕሮጀክቱን የመስመር ዝርጋታ የማጠናቀቅ ስራዎች መከናወናቸውንም ተናግረዋል።
ስራ አስኪያጁ አክለውም የውሃ ፕሮጀክቱ አሁን ላይ ተጨማሪ 20 ሊትር በሰከንድ ማመንጨት የሚችል መሆኑንና ይህም በልዩ ኢኮኖሚ ዞኑ ያለውን የውሃ አቅርቦት ጥራትና ተደራሽነት እንደሚያሻሽለው መግለጻቸውን ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026