የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>በግብርናው ዘርፍ የተነደፉ ፕሮግራሞች ያስገኙትን ተጨባጭ ውጤት ማስፋት ይገባል-ቋሚ ኮሚቴው</p>

Feb 6, 2025

IDOPRESS

ሀዋሳ፤ጥር 28/2017 (ኢዜአ):- በኢትዮጵያ በግብርናው ዘርፍ የተነደፉ ፕሮግራሞች ያስገኙትን ተጨባጭ ውጤት በሁሉም አካባቢዎች ማስፋት እንደሚገባ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስታወቀ።

የምክር ቤት አባላትን ጨምሮ የግብርና ሚኒስቴር፣ የፌዴራልና የክልል ባለድርሻ አካላት በሲዳማ ክልል ሁለት ወረዳዎች እየተከናወነ ያለውን የመስኖ ልማት ስራ ተመልክተዋል።

በህዝብ በተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን ላሌ በወቅቱ እንደገለጹት፥ የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ የተነደፉ አዳዲስ ኢንሼቲቮች ዘርፈ ብዙ ውጤት እያስመዘገቡ ነው።


በተለይም በግብርናው ዘርፍ የተነደፉ ፕሮግራሞች ተጨባጭ ለውጥ እያመጡ መሆናቸውን አንስተው ለውጡን በሁሉም አካባቢዎች በማስፋት በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና መጫወት ይገባል ብለዋል።

በአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም በሰብል ልማት በተለያዩ የሃገሪቱ አካባቢዎች የሚከናወኑ የልማት ስራዎች የአርሶአደሩን ህይወት የሚቀይሩና ከድህነት ለመውጣት የሚደረገውን ትግል የሚያግዙ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በሲዳማ ክልል በሆርቲካልቸር ዘርፍ አትክልትና ፍራፍሬን በመስኖ በማልማት የተገኘው ውጤት ለሌሎች ተሞክሮ የሚሆን መሆኑን ጠቅሰዋል።

በተለይም ዝናብ አጠር በሆነው ሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ በመስኖ የሚለማው መሬት የአርሶ አደሩን የምግብ ዋስትና በማረጋገጥ አካባቢውን ከአየር ንብረት ለውጥ ተጽእኖ የታደገ ነው ብለዋል።


የሲዳማ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ ሃላፊ አቶ መምሩ ሞኬ በክልሉ በዘንድሮ የበጋ መስኖ ከ72 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በሁለት ዙር በሚከናወነው የመስኖ ልማት ስራ የቤተሰብ ብልጽግና ለማረጋገጥ የተቀመጡ ፓኬጆችን መሰረት ያደረገና በዋናነት በአምስት የአትክልት ልማት ዘርፎች ላይ ትኩረት ያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

ለዚህም በ25 ወረዳዎች 581 በላይ ክላስተሮችን በማደራጀት ከ22 ሺህ በላይ ሄክታሩ የመስኖ ልማት ስራ በኩታገጠም የሚለማ መሆኑን ገልጸዋል።

ለመስኖ ልማት ስራ በቂ ግብዓት መቅረቡን የጠቀሱት አቶ መምሩ "ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶችን ጨምሮ ሌሎች የውሃ አማራጮችን በመጠቀም እየተከናወነ ያለው ስራ ውጤታማ ነው" ብለዋል።

የመስኖ ልማት ስራው ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በመሬት ሽፋንና ምርት፣ እንዲሁም ለድጋፍና ክትትል ምቹ በሆነው የኩታገጠም ስራ የተሻለ መሆኑን ገልጸዋል።

በሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ሃጊርሶ ደበላ በበኩላቸው በ12 ሄክታር መሬት ላይ ቲማቲም ጨምሮ የተለያዩ አትክልቶችን በመስኖ እያለሙ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በመስኖ ልማት ስራው ለበርካታ ወገኖች የስራ እድል ከመፍጠር ባሻገር ገበያን ማረጋጋት የሚያስችል ምርት እያመረቱ መሆኑን ገልጸዋል።

በመስክ ምልከታው ላይ የግብርና ሚኒስቴር የስራ ሀላፊዎች፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትና ከተለያዩ ክልሎች የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026