የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>በግብርናው ዘርፍ የተነደፉ ፕሮግራሞች ያስገኙትን ተጨባጭ ውጤት ማስፋት ይገባል-ቋሚ ኮሚቴው</p>

Feb 6, 2025

IDOPRESS

ሀዋሳ፤ጥር 28/2017 (ኢዜአ):- በኢትዮጵያ በግብርናው ዘርፍ የተነደፉ ፕሮግራሞች ያስገኙትን ተጨባጭ ውጤት በሁሉም አካባቢዎች ማስፋት እንደሚገባ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስታወቀ።

የምክር ቤት አባላትን ጨምሮ የግብርና ሚኒስቴር፣ የፌዴራልና የክልል ባለድርሻ አካላት በሲዳማ ክልል ሁለት ወረዳዎች እየተከናወነ ያለውን የመስኖ ልማት ስራ ተመልክተዋል።

በህዝብ በተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን ላሌ በወቅቱ እንደገለጹት፥ የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ የተነደፉ አዳዲስ ኢንሼቲቮች ዘርፈ ብዙ ውጤት እያስመዘገቡ ነው።


በተለይም በግብርናው ዘርፍ የተነደፉ ፕሮግራሞች ተጨባጭ ለውጥ እያመጡ መሆናቸውን አንስተው ለውጡን በሁሉም አካባቢዎች በማስፋት በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና መጫወት ይገባል ብለዋል።

በአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም በሰብል ልማት በተለያዩ የሃገሪቱ አካባቢዎች የሚከናወኑ የልማት ስራዎች የአርሶአደሩን ህይወት የሚቀይሩና ከድህነት ለመውጣት የሚደረገውን ትግል የሚያግዙ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በሲዳማ ክልል በሆርቲካልቸር ዘርፍ አትክልትና ፍራፍሬን በመስኖ በማልማት የተገኘው ውጤት ለሌሎች ተሞክሮ የሚሆን መሆኑን ጠቅሰዋል።

በተለይም ዝናብ አጠር በሆነው ሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ በመስኖ የሚለማው መሬት የአርሶ አደሩን የምግብ ዋስትና በማረጋገጥ አካባቢውን ከአየር ንብረት ለውጥ ተጽእኖ የታደገ ነው ብለዋል።


የሲዳማ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ ሃላፊ አቶ መምሩ ሞኬ በክልሉ በዘንድሮ የበጋ መስኖ ከ72 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በሁለት ዙር በሚከናወነው የመስኖ ልማት ስራ የቤተሰብ ብልጽግና ለማረጋገጥ የተቀመጡ ፓኬጆችን መሰረት ያደረገና በዋናነት በአምስት የአትክልት ልማት ዘርፎች ላይ ትኩረት ያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

ለዚህም በ25 ወረዳዎች 581 በላይ ክላስተሮችን በማደራጀት ከ22 ሺህ በላይ ሄክታሩ የመስኖ ልማት ስራ በኩታገጠም የሚለማ መሆኑን ገልጸዋል።

ለመስኖ ልማት ስራ በቂ ግብዓት መቅረቡን የጠቀሱት አቶ መምሩ "ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶችን ጨምሮ ሌሎች የውሃ አማራጮችን በመጠቀም እየተከናወነ ያለው ስራ ውጤታማ ነው" ብለዋል።

የመስኖ ልማት ስራው ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በመሬት ሽፋንና ምርት፣ እንዲሁም ለድጋፍና ክትትል ምቹ በሆነው የኩታገጠም ስራ የተሻለ መሆኑን ገልጸዋል።

በሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ሃጊርሶ ደበላ በበኩላቸው በ12 ሄክታር መሬት ላይ ቲማቲም ጨምሮ የተለያዩ አትክልቶችን በመስኖ እያለሙ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በመስኖ ልማት ስራው ለበርካታ ወገኖች የስራ እድል ከመፍጠር ባሻገር ገበያን ማረጋጋት የሚያስችል ምርት እያመረቱ መሆኑን ገልጸዋል።

በመስክ ምልከታው ላይ የግብርና ሚኒስቴር የስራ ሀላፊዎች፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትና ከተለያዩ ክልሎች የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026