የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>ባዛርና ኤግዚቢሽኑ ማህበራት ምርቶቻቸውን ከማስተዋወቅ ባሻገር እርስ በእርስ የገበያ ትስስር የሚፈጥሩበት ነው</p>

Feb 7, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 29/2017(ኢዜአ)፡- ባዛርና ኤግዚቢሽኑ ማህበራት ምርቶቻቸውን ከማስተዋወቅ ባሻገር እርስ በእርስ የገበያ ትስስር የሚፈጥሩበት ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጃንጥራር አባይ ገለጹ፡፡

ሀገር አቀፍ የህብረት ስራ ማህበራት ኤግዚቢሽንና ባዛር ዛሬ "የህብረት ስራ ማህበራት ሚና ለኢትዮጵያ ብልጽግና" በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል ተከፍቷል።


በመክፈቻ ስነ-ስርዓቱ የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጃንጥራር አባይ፣ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሰለሞን ላሌ፣ የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ሶፊያ ካሳ(ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ ህብረት ስራ ማህበራት ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ሽጉጤ፣ የከተማ አስተዳደሩ የስራ ሃላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።


አቶ ጃንጥራር አባይ በዚሁ ወቅት፤ በአዲስ አበባ ከተማ 2 ሚሊዮን አባላት ያሏቸው ከ 9 ሺህ በላይ ማህበራት እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡

እነዚህ ማህበራት ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለሸማቾች በማቅረብ ለዋጋ ንረት መረጋጋት አወንታዊ ሚና እየተጫቱ እንደሚገኙም ጠቅሰዋል፡፡

በዛሬው እለት የተከፈተው ኤግዚቢሽንና ባዛር ማህበራት ምርቶቻቸውን ከማስተዋወቅ ባሻገር እርስ በእርስ የገበያ ትስስር መፍጠር የሚያግዛቸው መሆኑንም ተናግረዋል።

ዝግጅቱ የታለመለትን ግብ እንዲመታ ከተማ አስተዳደሩ አስፈላጊውን ድጋፍ የሚያደርግ መሆኑንም አረጋግጠዋል፡፡


የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ሶፊያ ካሳ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ህብረት ስራ ማህበራት የበለጸገች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ለሚደረገው ርብርብ ትልቅ አቅም ናቸው ብለዋል፡፡

በመሆኑም መንግስት ህብረት ስራ ማህበራትን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር በትኩረት የሚሰራ መሆኑን ነው የተናገሩት፡፡

ዛሬ የተጀመረው ኤግዚቢሽንና ባዛር አዲስ አበባ ከተማንና ክልሎችን በንግድ ለማስተሳሰር ትልቅ እድል እንዳለውም አመላክተዋል፡፡


ህብረት ስራ ማህበራት አምራቹንና ሸማቹን የሚያገናኙ ድልድዮች መሆናቸውን የገለጹት ደግሞ የኢትዮጵያ ህብረት ስራ ማህበራት ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ሽጉጤ ናቸው፡፡

ማህበራቱ አምራቹንና ሸማቹን ከማገናኘት ባሻገር ለፋይናንስ ተደራሽነትና ለስራ እድል ፈጠራ ትልቅ ድርሻ እንዳላቸው ገልጸዋል፡፡

ዘርፉን ለማጠናከር የሪፎርም ስራ እንዲሰራ መደረጉንም ጨምረው አንስተዋል።

ኤግዚቢሽንና ባዛሩ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ11ኛ ጊዜ፤ በከተማ ደረጃ ደግሞ ለ4ኛ ጊዜ የሚካሄድ ሲሆን እስከ የካቲት 3 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ይቆያል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026