የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>ባዛርና ኤግዚቢሽኑ ማህበራት ምርቶቻቸውን ከማስተዋወቅ ባሻገር እርስ በእርስ የገበያ ትስስር የሚፈጥሩበት ነው</p>

Feb 7, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 29/2017(ኢዜአ)፡- ባዛርና ኤግዚቢሽኑ ማህበራት ምርቶቻቸውን ከማስተዋወቅ ባሻገር እርስ በእርስ የገበያ ትስስር የሚፈጥሩበት ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጃንጥራር አባይ ገለጹ፡፡

ሀገር አቀፍ የህብረት ስራ ማህበራት ኤግዚቢሽንና ባዛር ዛሬ "የህብረት ስራ ማህበራት ሚና ለኢትዮጵያ ብልጽግና" በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል ተከፍቷል።


በመክፈቻ ስነ-ስርዓቱ የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጃንጥራር አባይ፣ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሰለሞን ላሌ፣ የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ሶፊያ ካሳ(ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ ህብረት ስራ ማህበራት ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ሽጉጤ፣ የከተማ አስተዳደሩ የስራ ሃላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።


አቶ ጃንጥራር አባይ በዚሁ ወቅት፤ በአዲስ አበባ ከተማ 2 ሚሊዮን አባላት ያሏቸው ከ 9 ሺህ በላይ ማህበራት እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡

እነዚህ ማህበራት ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለሸማቾች በማቅረብ ለዋጋ ንረት መረጋጋት አወንታዊ ሚና እየተጫቱ እንደሚገኙም ጠቅሰዋል፡፡

በዛሬው እለት የተከፈተው ኤግዚቢሽንና ባዛር ማህበራት ምርቶቻቸውን ከማስተዋወቅ ባሻገር እርስ በእርስ የገበያ ትስስር መፍጠር የሚያግዛቸው መሆኑንም ተናግረዋል።

ዝግጅቱ የታለመለትን ግብ እንዲመታ ከተማ አስተዳደሩ አስፈላጊውን ድጋፍ የሚያደርግ መሆኑንም አረጋግጠዋል፡፡


የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ሶፊያ ካሳ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ህብረት ስራ ማህበራት የበለጸገች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ለሚደረገው ርብርብ ትልቅ አቅም ናቸው ብለዋል፡፡

በመሆኑም መንግስት ህብረት ስራ ማህበራትን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር በትኩረት የሚሰራ መሆኑን ነው የተናገሩት፡፡

ዛሬ የተጀመረው ኤግዚቢሽንና ባዛር አዲስ አበባ ከተማንና ክልሎችን በንግድ ለማስተሳሰር ትልቅ እድል እንዳለውም አመላክተዋል፡፡


ህብረት ስራ ማህበራት አምራቹንና ሸማቹን የሚያገናኙ ድልድዮች መሆናቸውን የገለጹት ደግሞ የኢትዮጵያ ህብረት ስራ ማህበራት ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ሽጉጤ ናቸው፡፡

ማህበራቱ አምራቹንና ሸማቹን ከማገናኘት ባሻገር ለፋይናንስ ተደራሽነትና ለስራ እድል ፈጠራ ትልቅ ድርሻ እንዳላቸው ገልጸዋል፡፡

ዘርፉን ለማጠናከር የሪፎርም ስራ እንዲሰራ መደረጉንም ጨምረው አንስተዋል።

ኤግዚቢሽንና ባዛሩ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ11ኛ ጊዜ፤ በከተማ ደረጃ ደግሞ ለ4ኛ ጊዜ የሚካሄድ ሲሆን እስከ የካቲት 3 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ይቆያል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026