የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>በኦሮሚያ ክልል በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የታቀደውን ለማሳካት ጠንካራ ድጋፍና ክትትል እየተደረገ ነው</p>

Feb 8, 2025

IDOPRESS

ጥር 30/2017(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የታቀደውን ለማሳካት ጠንካራ ድጋፍና ክትትል እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ በሪሶ ፈይሳ ለኢዜአ እንዳሉት የክልሉ መንግስት እርሻውን ለማዘመንና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ ነው።

ለዚህም ቢሮው አርሶ አደሩ የዝናብ ወቅትን ብቻ ከመጠበቅ ወጥቶ የውኃ አማራጮችን በመጠቀምበዓመት ሶስት ጊዜ ማምረት እንዲለምድና የሥራ ባህሉም እንዲለወጥ በየደረጃው ባሉ የዘርፉ አመራር አባላትና ባለሙያዎቹ ጠንካራ ድጋፍና ክትትል እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የአፈር ማዳበሪያን ጨምሮ የምርጥ ዘር፣ የተባይ ማጥፊያ፣ የአረም መከላከያና ሌሎች ግብዓቶችን የማሟላት ተግባራትን በጥናት ለይቶ በመተግበር ላይ መሆኑን ተናግረዋል።

በተለይም ለአርሶ አደሩ ድጋፍ በማድረግና በየደረጃው ያሉ ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ የተሻለ ውጤት መምጣቱን አብራርተዋል።

በዚህም በዘንድሮው የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት አራት ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን ታቅዶ በእስካሁኑ እንቅስቃሴ 3 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዘር መሸፈኑን ምክትል ሃላፊው ገልጸዋል።

በልማቱ የአርሶ አደሩ ፍላጎት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመምጣቱ የአርሶ አደሩን የስራ ባህል ከመቀየርና ገቢያቸውን ከማሳደግ አንፃር ክፍተኛ ሚና ስላለው የመነቃቃት ስሜት ፈጥሮባቸዋል ብለዋል።

አርሶ አደሮቹ የበጋ መስኖ ስንዴውን መደበኛ ስራቸው አድርገው እንዲሰሩ በቅርበት እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።

በዚህም በክልሉ በሁሉም ዞኖች እንዲሁም በከተማ አስተዳደሮች ጭምር ልማቱ በስፋት እየተከናወነ መሆኑን አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.