
ጥር 30/2017(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የታቀደውን ለማሳካት ጠንካራ ድጋፍና ክትትል እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ በሪሶ ፈይሳ ለኢዜአ እንዳሉት የክልሉ መንግስት እርሻውን ለማዘመንና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ ነው።
ለዚህም ቢሮው አርሶ አደሩ የዝናብ ወቅትን ብቻ ከመጠበቅ ወጥቶ የውኃ አማራጮችን በመጠቀምበዓመት ሶስት ጊዜ ማምረት እንዲለምድና የሥራ ባህሉም እንዲለወጥ በየደረጃው ባሉ የዘርፉ አመራር አባላትና ባለሙያዎቹ ጠንካራ ድጋፍና ክትትል እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የአፈር ማዳበሪያን ጨምሮ የምርጥ ዘር፣ የተባይ ማጥፊያ፣ የአረም መከላከያና ሌሎች ግብዓቶችን የማሟላት ተግባራትን በጥናት ለይቶ በመተግበር ላይ መሆኑን ተናግረዋል።
በተለይም ለአርሶ አደሩ ድጋፍ በማድረግና በየደረጃው ያሉ ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ የተሻለ ውጤት መምጣቱን አብራርተዋል።
በዚህም በዘንድሮው የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት አራት ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን ታቅዶ በእስካሁኑ እንቅስቃሴ 3 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዘር መሸፈኑን ምክትል ሃላፊው ገልጸዋል።
በልማቱ የአርሶ አደሩ ፍላጎት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመምጣቱ የአርሶ አደሩን የስራ ባህል ከመቀየርና ገቢያቸውን ከማሳደግ አንፃር ክፍተኛ ሚና ስላለው የመነቃቃት ስሜት ፈጥሮባቸዋል ብለዋል።
አርሶ አደሮቹ የበጋ መስኖ ስንዴውን መደበኛ ስራቸው አድርገው እንዲሰሩ በቅርበት እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።
በዚህም በክልሉ በሁሉም ዞኖች እንዲሁም በከተማ አስተዳደሮች ጭምር ልማቱ በስፋት እየተከናወነ መሆኑን አንስተዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026