
ጥር 30/2017(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የታቀደውን ለማሳካት ጠንካራ ድጋፍና ክትትል እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ በሪሶ ፈይሳ ለኢዜአ እንዳሉት የክልሉ መንግስት እርሻውን ለማዘመንና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ ነው።
ለዚህም ቢሮው አርሶ አደሩ የዝናብ ወቅትን ብቻ ከመጠበቅ ወጥቶ የውኃ አማራጮችን በመጠቀምበዓመት ሶስት ጊዜ ማምረት እንዲለምድና የሥራ ባህሉም እንዲለወጥ በየደረጃው ባሉ የዘርፉ አመራር አባላትና ባለሙያዎቹ ጠንካራ ድጋፍና ክትትል እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የአፈር ማዳበሪያን ጨምሮ የምርጥ ዘር፣ የተባይ ማጥፊያ፣ የአረም መከላከያና ሌሎች ግብዓቶችን የማሟላት ተግባራትን በጥናት ለይቶ በመተግበር ላይ መሆኑን ተናግረዋል።
በተለይም ለአርሶ አደሩ ድጋፍ በማድረግና በየደረጃው ያሉ ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ የተሻለ ውጤት መምጣቱን አብራርተዋል።
በዚህም በዘንድሮው የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት አራት ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን ታቅዶ በእስካሁኑ እንቅስቃሴ 3 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዘር መሸፈኑን ምክትል ሃላፊው ገልጸዋል።
በልማቱ የአርሶ አደሩ ፍላጎት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመምጣቱ የአርሶ አደሩን የስራ ባህል ከመቀየርና ገቢያቸውን ከማሳደግ አንፃር ክፍተኛ ሚና ስላለው የመነቃቃት ስሜት ፈጥሮባቸዋል ብለዋል።
አርሶ አደሮቹ የበጋ መስኖ ስንዴውን መደበኛ ስራቸው አድርገው እንዲሰሩ በቅርበት እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።
በዚህም በክልሉ በሁሉም ዞኖች እንዲሁም በከተማ አስተዳደሮች ጭምር ልማቱ በስፋት እየተከናወነ መሆኑን አንስተዋል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026