አዲስ አበባ፤የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፦ለአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ለሚመጡ እንግዶች ቀልጣፋ የቴሌኮም እና የባንክ አገልግሎቶችን ለመስጠት መዘጋጀታቸውን ኢትዮ- ቴሌኮም እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስታወቁ።
38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የካቲት 8 እና 9/2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ የሚካሄድ ሲሆን አገልግሎት ሰጪ ተቋማትም አስፈላጊውን ዝግጅት ማጠናቀቃቸው ተገልጿል።
ከአገልግሎት ሰጪ ተቋማት መካከል ኢዜአ ያነጋገራቸው ኢትዮ-ቴሌኮም እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለህብረቱ ጉባኤ ለሚመጡ እንግዶች ቀልጣፋና ምቹ አገልግሎት ለመስጠት መዘጋጀታቸውን ጠቅሰዋል።
የኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ኮሙኒኬሽን ኦፊሰር መሳይ ውብሽት፤ እንግዶች ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ከመድረሳቸው ጀምሮ የቴሌኮም አገልግሎት እንዲያገኙ ለማድረግ በቂ ዝግጅት መደረጉን ገልጸዋል።
በሚያርፉባቸው ሆቴሎችና በህብረቱ ዋና መስሪያ ቤትም የአገልግሎት መስጫ ማዕከላትን በማቋቋም የሲም ካርድና የኢንተርኔት አገልግሎቶችን በቀላሉ የሚያገኙበት ሥርዓት ከወዲሁ መዘርጋቱን ተናግረዋል።
የኢትዮ-ቴሌኮም የአገልግሎቶች ማረጋገጫ ቺፍ ኦፊሰር አበበ ያንባው፤ በህብረቱ ጉባኤ ለመታደም የሚመጡ እንግዶች በቆይታቸው ከኔትወርክ ጋር የተያያዘ የቴክኒክ ችግር እንዳያጋጥማቸው በቂ ዝግጅት አድርገናል ብለዋል።
ለዚህም አስተማማኝ የ4 ጂ እና 5 ጂ ኔትወርክ በጥራት እንዲያገኙ በዋና ዋና ማዕከላት ማሻሻያ ስራ መከናወኑን ተናግረዋል።
የአገልግሎት መቋረጥ እንዳይፈጠር አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል የሚያደርግ የባለሙያ ስምሪት መሰጠቱን ገልጸዋል።
በሌላ በኩል እንግዶች በቆይታቸው ቀልጣፋ የባንክ አገልግሎቶችን እንዲያገኙ ዝግጅት መደረጉን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ገልጿል።
በባንኩ የዲጂታል ባንኪንግ ዲቪዥን መርቻንትና ኤጀንት ማኔጅመንት ዳይሬክተር ብሌን ኃይለ ሚካኤል፤ የሚያስፈልጋቸውን የውጭ ምንዛሬ እንዲፈጽሙ ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ተናግረዋል።
ከዚህ በተጨማሪ በሆቴሎችም የፖስ እና ሌሎች የዲጂታል ባንኪንግ አማራጮችን በመጠቀም ግብይትና ክፍያ የሚፈጽሙበት ዕድል መፈጠሩን ነው ያነሱት።
አዲስ አበባ ፤የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርት ተገልጋዮች ፋይዳ መታወቂያን ተጠቅመው በዲጂታል አማራጭ ትኬት የሚቆርጡበት አሰራር ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 03/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የለማ የትራንስፖርት ኦፕሬተሮችንና የጭነት ባለቤቶችን የሚገናኝ መተግበሪያ አስጀምሯል። ...
Feb 12, 2025