አዲስ አበባ፤ የካቲት 02/2017(ኢዜአ)፦ የዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋም (አይኤምኤፍ) ማኔጂንግ ዳይሬክተር ክርስታሊና ጂኦርጂዬቫ የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጎብኝተዋል።
ማኔጂንግ ዳይሬክተሯ ከገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ፣ ከብሔራዊ ባንክ ገዢ ማሞ ምህረቱ፣ ከፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር) እና ከሌሎች የመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር የአድዋ ድል መታሰቢያን ጎብኝተዋል።
ክርስታሊና ጂኦርጂዬቫ በኢትዮጵያ በሚኖራቸው የስራ ቆይታ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ጋር በኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት፣ ቅድሚያ በሚሰጣቸው ፖሊሲዎች፣ በኢኮኖሚ ማሻሻያዎችና በግሉ ዘርፍ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ዕድሎች ላይ ውይይት እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።
የኢትዮጵያ የስራ ጉብኝታቸውም አይኤምኤፍ የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ልማት ለመደገፍ እና የፖሊሲ ምክክሮችን በማድረግ የማይበገር እና ዘላቂ ሀገራዊ ብልጽግናን ለማምጣት ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑ ተመላክቷል።
ማኔጂንግ ዳይሬክተሯ በትላንትናው ዕለት ብሔራዊ ቤተ መንግሥትን፣ ለነገዋ የሴቶች ተሃድሶና የክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከልን እና ብርሃን የዓይነ ስውራን አዳሪ ትምህርት ቤትን መጎብኘታቸው ይታወቃል።
አዲስ አበባ ፤የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርት ተገልጋዮች ፋይዳ መታወቂያን ተጠቅመው በዲጂታል አማራጭ ትኬት የሚቆርጡበት አሰራር ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 03/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የለማ የትራንስፖርት ኦፕሬተሮችንና የጭነት ባለቤቶችን የሚገናኝ መተግበሪያ አስጀምሯል። ...
Feb 12, 2025