የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>ኢንስቲትዩቱ የጂኦስፓሻል መረጃዎችን የሚመዘግብና የሚያጋራ ዲጂታል የመረጃ ቋት(portal) በይፋ ስራ አስጀመረ</p>

Feb 11, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 3/2017(ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ እና የጂኦስፓሻል ኢኒስቲትዩት የመሬትና መሬት ነክ መረጃዎችን የሚመዘግብና የሚያጋራ ዲጅታል የመረጃ ቋት(Portal) በይፋ ስራ አስጀመረ፡፡

ከኢንስቲትዩቱ ተልዕኮ አንዱ ሀገራዊ የጂኦስፓሻል መረጃ መሰረተ ልማት በመዘርጋት አስቻይ የጂኦስፓሻል ኢንፎርሜሽንና ቴክኖሎጂ ስርዓተ ምህዳር መፍጠር ነው።

በዚህም መሰረት የጂኦስፓሻል ዳታ መሰረተ ልማት በመዘርጋት ሀገራዊ የመሬት መረጃ አስተዳደርና ስርጭትን የሚያሳልጥ(ESRI Enterprise Portal) ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ወደ ስራ አስገብቷል።


የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ይሽሩን አለማየሁ(ዶ/ር)፥ ኢትዮጵያ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን እውን ለማድረግ ስትራቴጂ ቀርጻ እየሰራች መሆኗን አንስተዋል።

ይህ ስትራቴጂ የሀገሪቱ የልማት እቅድ ዋነኛ ምሰሶ መሆኑን ጠቅሰው፥ በዲጂታል ቴክኖሎጂ በቂ ዕውቀትና ክህሎት ያለው ማህበረሰብ ማፍራት ለሀገሪቱ ምጣኔ ሃብት ዕድገት ጉልህ ሚና እንደሚጫወት ጠቁመዋል።

ዛሬ ይፋ የሆነው ዲጂታል የጂኦስፓሻል ፖርታል በኢትዮጵያ የመሬት መረጃዎችን የመሰብሰብ፣ የማስተዳደር፣ የማጋራትና የመጠቀም አቅምን በእጅጉ የሚያሻሽል ነው ብለዋል።

የጂኦስፓሻል መረጃዎች ለውሳኔ ሰጪዎች ወሳኝ እንደሆኑ ጠቅሰው፥ በተለይም በከተማ ፕላን፣ በግብርና፣ በአደጋ ስጋት አመራር እና በአካባቢ ጥበቃ ስራ ላይ ጉልህ አበርክቶ እንደሚኖራቸው ነው የገለጹት።

በቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎትና የልማት ሥራን ለማፋጠን የመረጃ አያያዝ ስርዓት ወሳኝ ሚና እንዳለው ጠቅሰው፥ በዚህ ረገድ ፖርታሉ ትልቅ እመርታን እንደሚያመጣ ጠቁመዋል።

መንግሥት የዲጂታል መረጃ አያያዝና ስርጭትን በአግባቡ መምራት የሚያስችሉ ፖሊሲና ህግጋትን በማዘጋጀት ወደ ተግባር ማስገባቱንም አንስተዋል።


የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር በላቸው ፀሐይ እንደገለጹት፤ ዲጂታል መሰረተ ልማቱ የጂኦስፓሻል ዳታ መሰረተ ልማት ዝርጋታን እውን በማድረግ ሀገራዊ የመረጃ አስተዳደርና ስርጭትን የሚያሳልጥ ነው።

ዲጂታል መሰረተ ልማቱ የመንግስት አገልግሎት ሰጭ ተቋማትን የተናበበ የመረጃ አጠቃቀም እንደሚያጎለብትም አመላክተዋል፡፡

በመሬት ላይ ያለውን ማንኛውም ነገር መገኛውን ብቻ ሳይሆን ከማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መረጃዎች ጋር አቀናጅቶ በመተንተን ትክክለኛ ውሳኔን ለማሳለፍ ያስችላል ነው ያሉት።


የጀርመን የልማት ተራድኦ ድርጅት(ጂአይዜድ) የጂኦስፓሻል ፕሮጀክት አማካሪ ቱሉ በሻህ(ዶ/ር)፤ የመሰረተ ልማቱ ይፋ መሆን ዘላቂ የልማት ግቦችን ለማሳካት ጠቀሜታው ከፍ ያለ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በተለይም የመሬት አጠቃቀም እና ሌሎች ሀገራዊ የልማት እቅዶችን ለማሳካት ወሳኝ መሆኑን በመጥቀስ፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026