ጊምቢ/ጅማ፤ የካቲት 3/2017(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ወለጋ እና ጅማ ዞኖች የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት በግብርና ባለሙያዎች ድጋፍ እና ክትትል ታግዞ በተሻለ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን የየዞኖቹ ግብርና ጽህፈት ቤቶች አስታወቁ።
በምዕራብ ወለጋ ዞን ከ145 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታውቋል፡፡
የጽህፈት ቤቱ ሀላፊ አቶ ዳግም መላኩ ለኢዜአ አንደተናገሩት በዘንድሮ የበጋ ወራት ከ182 ሺህ ሄክታር ባላይ መሬት በበጋ መስኖ ስንዴ ለማልማት ታቅዶ እስካሁን 145 ሺህ 790 ሄክታር መሬት በዘር መሸፈኑን ተናግረዋል፡፡
በዘር ከተሸፈነው መሬትም ከ6 ነጥብ 9 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ስንዴ ለማምረት በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል፡፡
የታቀደውን ምርት ለማግኘትም የግብርና ባለሙያዎች ለአርሶ አደሩ ድጋፍና ክትትል ማድረጋቸውን ጠቅሰዋል፡፡
በግብአት አቅርቦት በኩል ከ442 ኩንታል በላይ ምርጥ ዘርና 43 ሺህ 121 ኩንታል የአፈር መዳበሪያ እንዲሁም የተፈጥሮ መዳበሪያ ጥቅም ላይ መዋሉን ተናግረዋል፡፡
ባለፉት ሶስት ዓመታት በበጋ የተተገበረው የበጋ መስኖ ስንዴ ማልማት የአርሶ አደሩን ኑሮ እየለወጠ መምጣቱን ጠቅሰዋል፡፡
የበጋ መስኖ ስንዴ ኢኒሼቲቭን ውጤታማ ለማድረግ በቅንጅት መሰራቱን የተናገሩት ደግሞ የጅማ ዞን ግብርና ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ቲጃኒ ተማም ናቸው።
የመስኖ ስንዴው በአረምና በተባይ እንዳይጠቃ ከ34 ሺህ ሊትር በላይ የጸረ አረም መድሀኒቶች ለአርሶ አደሩ ተደራሽ መደረጉን ተናግረዋል።
እስካሁን ከለማው መሬትም ከ11 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የስንዴ ምርት እንደሚጠበቅ አቶ ቲጃኒ አክለዋል።
በበጋ መስኖ ስንዴ የተሰማሩ የዞኑ አርሶ አደሮች በበኩላቸው ሰብሉን ከአረምና ከጸረ ሰብል በሽታዎች ለመከላከል እየሰራን ነው ብለዋል።
በምዕራብ ወለጋ ዞን የበጊ ወረዳ አርሶ አደር ኑረዲን ከማል፤ ባለፉት አመታት ባለሙት የበጋ መስኖ ስንዴ ገቢያቸው በመጨመሩ በዘንድሮው አመት ግማሽ ሄክታር መሬታቸውን በስንዴ ማልማታቸውን ተናግረዋል፡፡
በዞኑ የጊምቢ ወረዳ አርሶ አደር ገላና ሶቦቃ፤ በበኩላቸው ሶስት ሆነው በኩታ ገጠም ሁለት ሄክታር የሚጠጋ መሬት በበጋ መስኖ ስንዴ እያለሙ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
አዲስ አበባ ፤የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርት ተገልጋዮች ፋይዳ መታወቂያን ተጠቅመው በዲጂታል አማራጭ ትኬት የሚቆርጡበት አሰራር ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 03/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የለማ የትራንስፖርት ኦፕሬተሮችንና የጭነት ባለቤቶችን የሚገናኝ መተግበሪያ አስጀምሯል። ...
Feb 12, 2025