የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>በዞኖቹ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት በግብርና ባለሙያዎች ድጋፍ እና ክትትል ታግዞ በተሻለ መልኩ እየተከናወነ ይገኛል</p>

Feb 11, 2025

IDOPRESS

ጊምቢ/ጅማ፤ የካቲት 3/2017(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ወለጋ እና ጅማ ዞኖች የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት በግብርና ባለሙያዎች ድጋፍ እና ክትትል ታግዞ በተሻለ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን የየዞኖቹ ግብርና ጽህፈት ቤቶች አስታወቁ።

በምዕራብ ወለጋ ዞን ከ145 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታውቋል፡፡

የጽህፈት ቤቱ ሀላፊ አቶ ዳግም መላኩ ለኢዜአ አንደተናገሩት በዘንድሮ የበጋ ወራት ከ182 ሺህ ሄክታር ባላይ መሬት በበጋ መስኖ ስንዴ ለማልማት ታቅዶ እስካሁን 145 ሺህ 790 ሄክታር መሬት በዘር መሸፈኑን ተናግረዋል፡፡


በዘር ከተሸፈነው መሬትም ከ6 ነጥብ 9 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ስንዴ ለማምረት በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል፡፡

የታቀደውን ምርት ለማግኘትም የግብርና ባለሙያዎች ለአርሶ አደሩ ድጋፍና ክትትል ማድረጋቸውን ጠቅሰዋል፡፡

በግብአት አቅርቦት በኩል ከ442 ኩንታል በላይ ምርጥ ዘርና 43 ሺህ 121 ኩንታል የአፈር መዳበሪያ እንዲሁም የተፈጥሮ መዳበሪያ ጥቅም ላይ መዋሉን ተናግረዋል፡፡

ባለፉት ሶስት ዓመታት በበጋ የተተገበረው የበጋ መስኖ ስንዴ ማልማት የአርሶ አደሩን ኑሮ እየለወጠ መምጣቱን ጠቅሰዋል፡፡


የበጋ መስኖ ስንዴ ኢኒሼቲቭን ውጤታማ ለማድረግ በቅንጅት መሰራቱን የተናገሩት ደግሞ የጅማ ዞን ግብርና ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ቲጃኒ ተማም ናቸው።

የመስኖ ስንዴው በአረምና በተባይ እንዳይጠቃ ከ34 ሺህ ሊትር በላይ የጸረ አረም መድሀኒቶች ለአርሶ አደሩ ተደራሽ መደረጉን ተናግረዋል።

እስካሁን ከለማው መሬትም ከ11 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የስንዴ ምርት እንደሚጠበቅ አቶ ቲጃኒ አክለዋል።

በበጋ መስኖ ስንዴ የተሰማሩ የዞኑ አርሶ አደሮች በበኩላቸው ሰብሉን ከአረምና ከጸረ ሰብል በሽታዎች ለመከላከል እየሰራን ነው ብለዋል።

በምዕራብ ወለጋ ዞን የበጊ ወረዳ አርሶ አደር ኑረዲን ከማል፤ ባለፉት አመታት ባለሙት የበጋ መስኖ ስንዴ ገቢያቸው በመጨመሩ በዘንድሮው አመት ግማሽ ሄክታር መሬታቸውን በስንዴ ማልማታቸውን ተናግረዋል፡፡

በዞኑ የጊምቢ ወረዳ አርሶ አደር ገላና ሶቦቃ፤ በበኩላቸው ሶስት ሆነው በኩታ ገጠም ሁለት ሄክታር የሚጠጋ መሬት በበጋ መስኖ ስንዴ እያለሙ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026