የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>የጎንደር ከተማን የመሬት መረጃ ሥርአት ለማዘመን የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ -መምሪያው</p>

Feb 11, 2025

IDOPRESS

ጎንደር፤ የካቲት 3/2017 (ኢዜአ)፡-የጎንደር ከተማን የመሬት ምዝገባ መረጃ ሥርአት በማዘመን የህዝቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመፍታት የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የከተማ አስተዳደሩ መሬት መምሪያ አስታወቀ፡፡

በከተማ መሬት ምዝገባና ባጋጠሙ ችግሮች ላይ ያተኮረ የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ ዛሬ በጎንደር ከተማ ተካሂዷል።

የመምሪያው ሃላፊ አቶ ትዛዙ በጽሃ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፤ የከተማውን የመሬት ምዝገባ መረጃ ሥርአት ለማዘመን የዲጂታላይዜሽን ትግበራ እየተከናወነ ነው፡፡


በሁለት ክፍለ ከተሞች ከ5 ሺህ በላይ በሚሆኑ ይዞታዎች የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መረጃዎችን በማሰባሰብ ወደ ኮምፒውተር የማስገባት ተግባራት መከናወናቸውን ጠቁመው፣ በቀጣይም ወደ አራት ክፍለ ከተሞች ለማስፋት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።

ዘመናዊ የመሬት መረጃ ሥርአት የከተማ መሬትን በአግባቡ በማስተዳደርና በመምራት ህገ ወጥ የመሬት ወረራርንና ሀሰተኛ ሰነዶችን ከመቆጣጠርና ከመከላከል ባለፈ ለከተማዋ ልማት የላቀ አስተዋጾ አለው ብለዋል፡፡

"በተጨማሪም በመሬት ይገባኛል ሳቢያ የሚፈጠሩ የወሰን ግጭቶችን በመፍታት ለህዝቡ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ፈጥኖ ምላሽ ለመስጠት ያስችላል" ብለዋል።

በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የከተማ አስተዳደሩ ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ሃላፊ አቶ ሙሉጌታ ታደሰ በበኩላቸው፣ የዲጂታላይዜሽን ትግበራው ከተሞችን ለማልማትና የገቢ አቅምን ለማሳደግ አስተዋጾ እንዳለው ነው የተናገሩት።

የምዝገባ ስርአቱ እንዲሳካ አጋር አካላት ለተግባራዊነቱ በቁርጠኝነት እንዲሰሩ አሳስበው፣ የከተማ አስተዳደሩ በበጀት፣ በሰው ሃይልና በቁሳቁስ ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል።

በምክክር መድረኩ ላይ የከተማ አስተዳደሩና የክፍለ ከተሞች አመራሮችን ጨምሮ ባለሙያዎችና አጋር አካላት መሳተፋቸው ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.