
ጎንደር፤ የካቲት 3/2017 (ኢዜአ)፡-የጎንደር ከተማን የመሬት ምዝገባ መረጃ ሥርአት በማዘመን የህዝቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመፍታት የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የከተማ አስተዳደሩ መሬት መምሪያ አስታወቀ፡፡
በከተማ መሬት ምዝገባና ባጋጠሙ ችግሮች ላይ ያተኮረ የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ ዛሬ በጎንደር ከተማ ተካሂዷል።
የመምሪያው ሃላፊ አቶ ትዛዙ በጽሃ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፤ የከተማውን የመሬት ምዝገባ መረጃ ሥርአት ለማዘመን የዲጂታላይዜሽን ትግበራ እየተከናወነ ነው፡፡

በሁለት ክፍለ ከተሞች ከ5 ሺህ በላይ በሚሆኑ ይዞታዎች የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መረጃዎችን በማሰባሰብ ወደ ኮምፒውተር የማስገባት ተግባራት መከናወናቸውን ጠቁመው፣ በቀጣይም ወደ አራት ክፍለ ከተሞች ለማስፋት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።
ዘመናዊ የመሬት መረጃ ሥርአት የከተማ መሬትን በአግባቡ በማስተዳደርና በመምራት ህገ ወጥ የመሬት ወረራርንና ሀሰተኛ ሰነዶችን ከመቆጣጠርና ከመከላከል ባለፈ ለከተማዋ ልማት የላቀ አስተዋጾ አለው ብለዋል፡፡
"በተጨማሪም በመሬት ይገባኛል ሳቢያ የሚፈጠሩ የወሰን ግጭቶችን በመፍታት ለህዝቡ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ፈጥኖ ምላሽ ለመስጠት ያስችላል" ብለዋል።
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የከተማ አስተዳደሩ ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ሃላፊ አቶ ሙሉጌታ ታደሰ በበኩላቸው፣ የዲጂታላይዜሽን ትግበራው ከተሞችን ለማልማትና የገቢ አቅምን ለማሳደግ አስተዋጾ እንዳለው ነው የተናገሩት።
የምዝገባ ስርአቱ እንዲሳካ አጋር አካላት ለተግባራዊነቱ በቁርጠኝነት እንዲሰሩ አሳስበው፣ የከተማ አስተዳደሩ በበጀት፣ በሰው ሃይልና በቁሳቁስ ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል።
በምክክር መድረኩ ላይ የከተማ አስተዳደሩና የክፍለ ከተሞች አመራሮችን ጨምሮ ባለሙያዎችና አጋር አካላት መሳተፋቸው ታውቋል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026