
የካቲት 5/2017(ኢዜአ)፦በሸገር ከተማ አስተዳደር የተለያዩ የውሃ አማራጮችን በመጠቀም ከ42 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በበጋ መስኖ እየለማ መሆኑን የከተማው መስኖ ልማት ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።
የጽሕፈት ቤቱ ሃላፊ አቶ አበራ ጫላ እንደገለጹት በከተማ አስተዳደሩ ለከተማ ግብርናም ሆነ ለበጋ መስኖ ልማት የሚያገለግል ውሃ ማቅረብ የሚያስችል ጥናት ተደርጓል።
በጥናቱ መሰረትም የአቅም ልየታ በማድረግ የገጸ ምድርና ከርሰ ምድር ውሃ በማቅረብ የመስኖ ልማት ስራ መጀመሩን ተናግረዋል።

በተለይም በከተማው በኩራ ጅዳ፣ ለገ ጣፎ፣ ለገ ዳዲ እና በሰበታ ክፍለ ከተሞች ለመስኖ ልማት የሚውሉ ውኃ መቅረቡን ለአብነት ጠቅሰዋል።
በዚህም በበጀት ዓመቱ 170 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ ውሃ በማቅረብ ከ42 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በበጋ መስኖ እየለማ መሆኑን አስታውቀዋል።

በከተማ አስተዳደሩ ከዚህ ቀደም የበጋ መስኖ ልማት እንደማይታወቅ አስታውሰው፤ ከተማው እንደ አዲስ ከተመሰረተ ወዲህ አርሶ አደሮችን በማሰልጠን ወደ ስራ መገባቱን ተናግረዋል።
በተለይም የውሃ ጉድጓዶችን በመቆፈር፣ ምንጮችን በማጎልበት፣ ወንዞችን በመጥለፍና የዝናብ ውሃን በማቆር ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ሲሰራ መቆየቱን አስረድተዋል።
በዚህም የዝናብ ውሃን ብቻ በመጠበቅ በዓመት አንዴ ሲያምርት የነበረው የአካባቢው አርሶ አደር በአሁኑ ወቅት የመስኖ ውሃን በመጠቀም በዓመት ሶስት ጊዜ ማምረት መቻሉን ተናግረዋል።
በከተማ አስተዳደሩ ስንዴ፣ አትክልትና ፍራፍሬን በበጋ መስኖ በብዛት በማልማት መቻሉንም ጠቅሰዋል።
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026