የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>በጉምሩክ ኮሚሽን የመቀሌ ቅርንጫፍ በቴክኖሎጂ በታገዘ የዲጂታል አሰራር ቀልጣፋ አገልግሎት እየሰጠ ነው</p>

Feb 13, 2025

IDOPRESS

መቀሌ፤ የካቲት 6/2017(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን የመቀሌ ቅርንጫፍ በቴክኖሎጂ የታገዘ የዲጂታል አሰራርን ተግባራዊ በማድረግ ለደንበኞቹ ቀልጣፋ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን አስታወቀ።

በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ስድስት ወራትም 2 ነጥብ 74 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱንም ገልጿል።

በኮሚሽኑ የመቀሌ ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ ምህረተአብ ገብረመድህን፤በቴክኖሎጂ የተደገፉ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እየተሰጠ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

ደንበኞች ከውጭ የሚያስገቧቸው እቃዎች አሰራሩንም ሆነ የቀረጥና መጋዘን አገልግሎትን ጨምሮ አጠቃላይ ክፍያውን በተመለከተ በአካል መምጣት ሳያስፈልጋቸው ባሉበት ሆነው የሚስተናገዱበት አሰራር መዘርጋቱን ገልጸዋል።

በዚህ አሰራር መሰረት የቅርንጫፉ ባለሙያዎች ለደንበኞች በቴክኖሎጂ የታገዘ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑንም አስረድተዋል።

የደንበኞች ንብረትም ከወደብ እስከ መዳረሻው በቴክኖሎጂ የታገዘ ክትትልና ቁጥጥር የሚደረግበት አሰራር ተገባራዊ ሆኗል ብለዋል።

በአገልግሎት አሰጣጡ የሚሰበሰበው ገንዘብ ከፍ ማለቱን አንስተው፤ በዚህም በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ስድስት ወራት ከእቅድ በላይ ገቢ መሰብሰቡን ተናግረዋል።

በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት 1 ነጥብ 77 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ የታቀደ ቢሆንም 2 ነጥብ 74 ቢሊዮን ብር ማሳካት ተችሏል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.