የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>በጉምሩክ ኮሚሽን የመቀሌ ቅርንጫፍ በቴክኖሎጂ በታገዘ የዲጂታል አሰራር ቀልጣፋ አገልግሎት እየሰጠ ነው</p>

Feb 13, 2025

IDOPRESS

መቀሌ፤ የካቲት 6/2017(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን የመቀሌ ቅርንጫፍ በቴክኖሎጂ የታገዘ የዲጂታል አሰራርን ተግባራዊ በማድረግ ለደንበኞቹ ቀልጣፋ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን አስታወቀ።

በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ስድስት ወራትም 2 ነጥብ 74 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱንም ገልጿል።

በኮሚሽኑ የመቀሌ ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ ምህረተአብ ገብረመድህን፤በቴክኖሎጂ የተደገፉ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እየተሰጠ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

ደንበኞች ከውጭ የሚያስገቧቸው እቃዎች አሰራሩንም ሆነ የቀረጥና መጋዘን አገልግሎትን ጨምሮ አጠቃላይ ክፍያውን በተመለከተ በአካል መምጣት ሳያስፈልጋቸው ባሉበት ሆነው የሚስተናገዱበት አሰራር መዘርጋቱን ገልጸዋል።

በዚህ አሰራር መሰረት የቅርንጫፉ ባለሙያዎች ለደንበኞች በቴክኖሎጂ የታገዘ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑንም አስረድተዋል።

የደንበኞች ንብረትም ከወደብ እስከ መዳረሻው በቴክኖሎጂ የታገዘ ክትትልና ቁጥጥር የሚደረግበት አሰራር ተገባራዊ ሆኗል ብለዋል።

በአገልግሎት አሰጣጡ የሚሰበሰበው ገንዘብ ከፍ ማለቱን አንስተው፤ በዚህም በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ስድስት ወራት ከእቅድ በላይ ገቢ መሰብሰቡን ተናግረዋል።

በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት 1 ነጥብ 77 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ የታቀደ ቢሆንም 2 ነጥብ 74 ቢሊዮን ብር ማሳካት ተችሏል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026

በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...

Mar 31, 2026