መቀሌ፤ የካቲት 6/2017(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን የመቀሌ ቅርንጫፍ በቴክኖሎጂ የታገዘ የዲጂታል አሰራርን ተግባራዊ በማድረግ ለደንበኞቹ ቀልጣፋ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን አስታወቀ።
በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ስድስት ወራትም 2 ነጥብ 74 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱንም ገልጿል።
በኮሚሽኑ የመቀሌ ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ ምህረተአብ ገብረመድህን፤በቴክኖሎጂ የተደገፉ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እየተሰጠ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
ደንበኞች ከውጭ የሚያስገቧቸው እቃዎች አሰራሩንም ሆነ የቀረጥና መጋዘን አገልግሎትን ጨምሮ አጠቃላይ ክፍያውን በተመለከተ በአካል መምጣት ሳያስፈልጋቸው ባሉበት ሆነው የሚስተናገዱበት አሰራር መዘርጋቱን ገልጸዋል።
በዚህ አሰራር መሰረት የቅርንጫፉ ባለሙያዎች ለደንበኞች በቴክኖሎጂ የታገዘ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑንም አስረድተዋል።
የደንበኞች ንብረትም ከወደብ እስከ መዳረሻው በቴክኖሎጂ የታገዘ ክትትልና ቁጥጥር የሚደረግበት አሰራር ተገባራዊ ሆኗል ብለዋል።
በአገልግሎት አሰጣጡ የሚሰበሰበው ገንዘብ ከፍ ማለቱን አንስተው፤ በዚህም በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ስድስት ወራት ከእቅድ በላይ ገቢ መሰብሰቡን ተናግረዋል።
በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት 1 ነጥብ 77 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ የታቀደ ቢሆንም 2 ነጥብ 74 ቢሊዮን ብር ማሳካት ተችሏል ብለዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026