መቀሌ፤ የካቲት 6/2017(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን የመቀሌ ቅርንጫፍ በቴክኖሎጂ የታገዘ የዲጂታል አሰራርን ተግባራዊ በማድረግ ለደንበኞቹ ቀልጣፋ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን አስታወቀ።
በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ስድስት ወራትም 2 ነጥብ 74 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱንም ገልጿል።
በኮሚሽኑ የመቀሌ ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ ምህረተአብ ገብረመድህን፤በቴክኖሎጂ የተደገፉ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እየተሰጠ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
ደንበኞች ከውጭ የሚያስገቧቸው እቃዎች አሰራሩንም ሆነ የቀረጥና መጋዘን አገልግሎትን ጨምሮ አጠቃላይ ክፍያውን በተመለከተ በአካል መምጣት ሳያስፈልጋቸው ባሉበት ሆነው የሚስተናገዱበት አሰራር መዘርጋቱን ገልጸዋል።
በዚህ አሰራር መሰረት የቅርንጫፉ ባለሙያዎች ለደንበኞች በቴክኖሎጂ የታገዘ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑንም አስረድተዋል።
የደንበኞች ንብረትም ከወደብ እስከ መዳረሻው በቴክኖሎጂ የታገዘ ክትትልና ቁጥጥር የሚደረግበት አሰራር ተገባራዊ ሆኗል ብለዋል።
በአገልግሎት አሰጣጡ የሚሰበሰበው ገንዘብ ከፍ ማለቱን አንስተው፤ በዚህም በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ስድስት ወራት ከእቅድ በላይ ገቢ መሰብሰቡን ተናግረዋል።
በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት 1 ነጥብ 77 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ የታቀደ ቢሆንም 2 ነጥብ 74 ቢሊዮን ብር ማሳካት ተችሏል ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026