
አሶሳ፤የካቲት 6/2017(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ ተግባራዊ የተደረገው አካታች የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ዘላቂና ቀጣይነት ያለው የምጣኔ ሃብት ዕድገት ለማስመዝገብ ጥሩ መሰረት ያኖረ መሆኑን በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የምጣኔ ሐብት መምህር ሙሐመድ ኢብራሂም ገለጹ።
በኢትዮጵያ የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ከሐምሌ 2016 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ መደረጉ ይታወቃል።
አጠቃላይ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሸያው ተግባራዊ በመደረጉም በአገሪቷ የወጪና ገቢ ንግድ ማነቆዎችን በመፍታት፤ የንግድ ሚዛንን በማስተካከል፤ የውጭ ምንዛሪ ግኝትን በማሳደግ የአገሪቷን የቆየ የኢኮኖሚ ስብራት ለመጠገን የሚያስችል መሆኑ ይነሳል።
በዚሁ ጉዳይ ላይ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የምጣኔ ሐብት መምህር ሙሐመድ ኢብራሂም፤ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሸያው የአገሪቷን ምጣኔ ሃብት ከውድቀት በመታደግ ዘላቂና አስተማማኝ እድገት እንዲኖር የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።
የግብርናው ዘርፍ ብቻውን የሀገሪቷን ኢኮኖሚ እንዲሸከም ተደርጎ መቆየቱ ለብዙ ችግሮች መዳረጉን አንስተው፥ ለውጡን ተከትሎ የተለያዩ ዘርፎች ዋና ዋና የእድገት ምሰሶዎች ተደርገው መወሰዳቸው ትልቅ እመርታ መሆኑን ተናግረዋል።
በመሆኑም በኢትዮጵያ ተግባራዊ የተደረገው አካታች የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ዘላቂና ቀጣይነት ያለው የምጣኔ ሃብት ዕድገት ለማስመዝገብ ጥሩ መሰረት ያኖረ ነው ብለዋል።
መንግስት የወሰደው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ከግብርናው ዘርፍ በተጨማሪ የአገልግሎት፣ የኢንዱስትሪ፣ የቱሪዝምና ሌሎች ዘርፎችን ያካተተ በመሆኑ የብዝሃ የኢኮኖሚ ዕድገት መሰረት ያስቀመጠ መሆኑንም አብራርተዋል።
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የሀገር ውስጥ ምርትን በማበረታታት፣ የወጭና ገቢ ንግድ ሚዛንን ለመጠበቅ፣የውጭ ምንዛሬ እጥረትን ለማቃለልና ኢንቨስትመንትን ለመሳብ ፍቱን መፍትሄ መሆኑንም አንስተዋል።
የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም የብድር አቅርቦት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ጤናማ መሆኑን አመላካች እንደሆነ ማሳያ መሆኑን አንስተዋል።
በቀጣይም የፋይናንስ ተቋማትን ማጠናከር፣የሥራ ዕድል ፈጠራን ማሳደግ እና የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ላይ በትኩረት መስራት ይገባል ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026