የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>ባለፉት ዓመታት ምቹ የኢንቨስትመንት ሁኔታን ለመፍጠር የተከናወነው ስራ አመርቂ ውጤት አስገኝቷል</p>

Feb 17, 2025

IDOPRESS

ጅግጅጋ፤ የካቲት 8/2017(ኢዜአ)፦በአገሪቱ ባለፉት ዓመታት ምቹ የኢንቨስትመንት ከባቢን ለመፍጠር የተከናወነው ስራ አመርቂ ውጤት ማምጣቱን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) ገለጹ።

የፌዴራል የክልልና ከተማ አስተዳደር የኢንቨስትመንት አስፈፃሚዎች የጋራ ምክክር መድረክ በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ በመካሄድ ላይ ነው።


የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን(ዶ/ር) በመድረኩ ላይ እንዳሉት ባለፉት ስድስት ዓመታት በዘርፉ የተከናወኑ የለውጥ ስራዎች ወደ ሁለንተናዊ ብልጽግና የሚወስዱ ምቹ መደላድሎችን ፈጥረዋል።

በተለይ ምቹ የኢንቨስትመንት ከባቢን ለመፍጠር የህግ ማዕቀፎችና ሌሎች የሪፎርም ስራዎች መከናወናቸውን አመልክተዋል።

በዚህም 85 የሚደርሱ የህግ፣ የፖሊሲ የሪፎርም ማሻሻያዎችና ማዕቀፎች ሲሰሩ መቆየታቸውን ጠቅሰው ይህም ለባለሃብቱ መደላደልን ከመፍጠር ባለፈ የኢትዮጵያን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ወደተሻለ ደረጃ ማድረስ አስችሏል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት አዋጅን የማሻሻል ስራም ለባለሃብቱ የዘርፍ ማስፋት ስራን ማምጣትንና በተለይም ቀደም ሲል የውጭ ባለሃብቶች በተወሰኑ ዘርፎች ላይ ብቻ የነበረው የኢንቨስትመንት እንቅሰቃሴ እንዲሰፋ ማስቻሉን ተናግረዋል።

ከዚህ ባለፈም ባለፉት ዓመታት ዝግ የነበሩ የጅምላ እና ችርቻሮ እንዲሁም የወጪና ገቢ ንግድ ስርዓት መንግስት በወሰደው ምቹ የኢንቨስትመንት ከባቢን የመፍጠር ስራ የውጪ ባለሀብቶች ወደ አገሪቱ እንዲገቡ ማስቻሉን አስረድተዋል።

በሌሎች ዘርፎች የተከናወኑ ስራዎች አበረታች መሆናቸውን የጠቀሱት ኮሚሽነሩ ይህም መንግስት በኢንቨስትመንት ዘርፉ ላይ ቁርጠኛ ስራ እያከናወነ መሆኑን ማሳያ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

መድረኩ ጠንካራ ስራዎችን ለማጎልበት፣ ውስንነቶችን በጋራ ለመቅረፍ እንዲሁም ሚናን ለይቶ ለመንቀሳቀስና ቅኝታዊ አሰራርን ለመዘርጋት ታቅዶ መዘጋጀቱን ተናግረዋል።


የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኢብራሂም ኡስማን በበኩላቸው መንግስት የአገሪቱ ልማት እንዲፋጠን በሰጠው ትኩረት አጥጋቢ ውጤት ማሰመዝገብ ተችሏል ብለዋል።

መንግስት ከሚያከናውናቸው መጠነ ሰፊ የልማት ስራዎች ባለፈ የባለሃብቱ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው ባለሃብቱ በኢንቨስትመንት ተሳትፎ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴውን እንዲያጎለብት ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ተናግረዋል።

በክልሉም ምቹ የኢንቨስትመንት ከባቢን ለመፍጠር የህግና የአሰራር ማሻሻያዎችን በማድረግ፣የተፋጠነ የመንግስት አገልግሎት በመስጠትና የብድር አገልግሎትን በማመቻቸት የግል ባለሃብቱ በአምራች እንዱትሪ ውስጥ እንዲሰማራ እየተደረገ መሆኑን አመልክተዋል።

ለሁለት ቀናት በተዘጋጀው የምክክር መድረክ ላይ የፌዴራል፣ የክልል እና የከተማ አስተዳደሮች የኢንቨትመንትና የኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026