
ጅግጅጋ፤ የካቲት 8/2017(ኢዜአ)፦በአገሪቱ ባለፉት ዓመታት ምቹ የኢንቨስትመንት ከባቢን ለመፍጠር የተከናወነው ስራ አመርቂ ውጤት ማምጣቱን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) ገለጹ።
የፌዴራል የክልልና ከተማ አስተዳደር የኢንቨስትመንት አስፈፃሚዎች የጋራ ምክክር መድረክ በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ በመካሄድ ላይ ነው።

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን(ዶ/ር) በመድረኩ ላይ እንዳሉት ባለፉት ስድስት ዓመታት በዘርፉ የተከናወኑ የለውጥ ስራዎች ወደ ሁለንተናዊ ብልጽግና የሚወስዱ ምቹ መደላድሎችን ፈጥረዋል።
በተለይ ምቹ የኢንቨስትመንት ከባቢን ለመፍጠር የህግ ማዕቀፎችና ሌሎች የሪፎርም ስራዎች መከናወናቸውን አመልክተዋል።
በዚህም 85 የሚደርሱ የህግ፣ የፖሊሲ የሪፎርም ማሻሻያዎችና ማዕቀፎች ሲሰሩ መቆየታቸውን ጠቅሰው ይህም ለባለሃብቱ መደላደልን ከመፍጠር ባለፈ የኢትዮጵያን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ወደተሻለ ደረጃ ማድረስ አስችሏል ብለዋል።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት አዋጅን የማሻሻል ስራም ለባለሃብቱ የዘርፍ ማስፋት ስራን ማምጣትንና በተለይም ቀደም ሲል የውጭ ባለሃብቶች በተወሰኑ ዘርፎች ላይ ብቻ የነበረው የኢንቨስትመንት እንቅሰቃሴ እንዲሰፋ ማስቻሉን ተናግረዋል።
ከዚህ ባለፈም ባለፉት ዓመታት ዝግ የነበሩ የጅምላ እና ችርቻሮ እንዲሁም የወጪና ገቢ ንግድ ስርዓት መንግስት በወሰደው ምቹ የኢንቨስትመንት ከባቢን የመፍጠር ስራ የውጪ ባለሀብቶች ወደ አገሪቱ እንዲገቡ ማስቻሉን አስረድተዋል።
በሌሎች ዘርፎች የተከናወኑ ስራዎች አበረታች መሆናቸውን የጠቀሱት ኮሚሽነሩ ይህም መንግስት በኢንቨስትመንት ዘርፉ ላይ ቁርጠኛ ስራ እያከናወነ መሆኑን ማሳያ ነው ሲሉ ተናግረዋል።
መድረኩ ጠንካራ ስራዎችን ለማጎልበት፣ ውስንነቶችን በጋራ ለመቅረፍ እንዲሁም ሚናን ለይቶ ለመንቀሳቀስና ቅኝታዊ አሰራርን ለመዘርጋት ታቅዶ መዘጋጀቱን ተናግረዋል።

የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኢብራሂም ኡስማን በበኩላቸው መንግስት የአገሪቱ ልማት እንዲፋጠን በሰጠው ትኩረት አጥጋቢ ውጤት ማሰመዝገብ ተችሏል ብለዋል።
መንግስት ከሚያከናውናቸው መጠነ ሰፊ የልማት ስራዎች ባለፈ የባለሃብቱ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው ባለሃብቱ በኢንቨስትመንት ተሳትፎ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴውን እንዲያጎለብት ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ተናግረዋል።
በክልሉም ምቹ የኢንቨስትመንት ከባቢን ለመፍጠር የህግና የአሰራር ማሻሻያዎችን በማድረግ፣የተፋጠነ የመንግስት አገልግሎት በመስጠትና የብድር አገልግሎትን በማመቻቸት የግል ባለሃብቱ በአምራች እንዱትሪ ውስጥ እንዲሰማራ እየተደረገ መሆኑን አመልክተዋል።
ለሁለት ቀናት በተዘጋጀው የምክክር መድረክ ላይ የፌዴራል፣ የክልል እና የከተማ አስተዳደሮች የኢንቨትመንትና የኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026