የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>የክልል ምክር ቤቱ ሰባት ረቂቅ አዋጆችን አፀደቀ</p>

Feb 17, 2025

IDOPRESS

አርባምንጭ፤ የካቲት 8/2017 (ኢዜአ):- የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት እያካሄደ ባለው መደበኛ ጉባኤ ሰባት ረቂቅ አዋጆችን አጸደቀ።

አዋጆቹ የኢንቨስትመንት አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ፣ የከተሞች ፈርጅ ለውጥ ረቂቅ አዋጅና ዝቅተኛ ተከፋይ የሆኑ የመንግስት ሠራተኞች ደምወዝ ማሻሻያ በጀት፣ የወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ ረቂቅ ማቋቋሚያ፣ የመስኖ ውሃ አጠቃቀም ረቂቅ አዋጅ፣ የበጎ ፈቃደኝነት ፖሊሲና የክልሉ ስንደቅ ዓላማና አርማ ረቂቅ አዋጆች ናቸው።

የምክር ቤቱ የፕላን፣ መሠረተ ልማትና የመንግስት ሀብት አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ዕንቁ ዮሐንስ የኢንቨስትመንት አስተዳደር አዋጅ ለክልሉ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ዕድገት ያለውን ሚና ይበልጥ ለማጎልበት ታስቦ መዘጋጀቱን አስረድተዋል።

የክልሉ ዕምቅ የተፈጥሮ ፀጋን ለኢኮኖሚ ዕድገት በማመቻቸት ቀጣይነት ያለው ዕድገት ለማምጣት ብሎም ሰፊ የሥራ ዕድል ለመፍጠር እንደሚያግዝ አስረድተዋል።

የከተሞች ፈርጅ ለውጥ ረቂቅ አዋጅ የከተሞች ሁለንተናዊ ልማት እንደሚበጅ ገልጽው፤ በአዋጁ መሰረት አርባምንጭ፣ ወላይታ ሶዶና ዲላ ከተሞች በሪጂኦ-ፖሊስ ፈርጅ እንዲመደቡ ተወስኗል።

የመንግስት ሠራተኞች ደመወዝ ማሻሻያ በጀት ለምክር ቤቱ የቀረበ ሲሆን ከፌዴራል መንግስት የተመደበውን 4 ቢሊዮን 204 ሚሊዮን 419 ሺህ 219 ብር በጀት ምክር ቤቱ አጽድቋል።

በተመሳሳይ የወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ ማቋቋሚያ፣ የመስኖ ውሃ ተጠቃሚዎች ማህበር፣ የበጎ ፈቃደኝነት ፖሊሲ እና የክልሉ ስንደቅ ዓላማና አርማ ረቂቅ አዋጆችም ጸድቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.