
አርባምንጭ፤ የካቲት 8/2017 (ኢዜአ):- የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት እያካሄደ ባለው መደበኛ ጉባኤ ሰባት ረቂቅ አዋጆችን አጸደቀ።
አዋጆቹ የኢንቨስትመንት አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ፣ የከተሞች ፈርጅ ለውጥ ረቂቅ አዋጅና ዝቅተኛ ተከፋይ የሆኑ የመንግስት ሠራተኞች ደምወዝ ማሻሻያ በጀት፣ የወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ ረቂቅ ማቋቋሚያ፣ የመስኖ ውሃ አጠቃቀም ረቂቅ አዋጅ፣ የበጎ ፈቃደኝነት ፖሊሲና የክልሉ ስንደቅ ዓላማና አርማ ረቂቅ አዋጆች ናቸው።
የምክር ቤቱ የፕላን፣ መሠረተ ልማትና የመንግስት ሀብት አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ዕንቁ ዮሐንስ የኢንቨስትመንት አስተዳደር አዋጅ ለክልሉ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ዕድገት ያለውን ሚና ይበልጥ ለማጎልበት ታስቦ መዘጋጀቱን አስረድተዋል።
የክልሉ ዕምቅ የተፈጥሮ ፀጋን ለኢኮኖሚ ዕድገት በማመቻቸት ቀጣይነት ያለው ዕድገት ለማምጣት ብሎም ሰፊ የሥራ ዕድል ለመፍጠር እንደሚያግዝ አስረድተዋል።
የከተሞች ፈርጅ ለውጥ ረቂቅ አዋጅ የከተሞች ሁለንተናዊ ልማት እንደሚበጅ ገልጽው፤ በአዋጁ መሰረት አርባምንጭ፣ ወላይታ ሶዶና ዲላ ከተሞች በሪጂኦ-ፖሊስ ፈርጅ እንዲመደቡ ተወስኗል።
የመንግስት ሠራተኞች ደመወዝ ማሻሻያ በጀት ለምክር ቤቱ የቀረበ ሲሆን ከፌዴራል መንግስት የተመደበውን 4 ቢሊዮን 204 ሚሊዮን 419 ሺህ 219 ብር በጀት ምክር ቤቱ አጽድቋል።
በተመሳሳይ የወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ ማቋቋሚያ፣ የመስኖ ውሃ ተጠቃሚዎች ማህበር፣ የበጎ ፈቃደኝነት ፖሊሲ እና የክልሉ ስንደቅ ዓላማና አርማ ረቂቅ አዋጆችም ጸድቀዋል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026