
አርባምንጭ፤ የካቲት 8/2017(ኢዜአ)፡- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ባለፉት ስድስት ወራት የትምህርትና የጤና ልማት ሥራዎች ውጤት መመዝገቡን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት 4ኛ መደበኛ ጉባኤ በክልሉ መንግስት በተከናወኑ የግማሽ ዓመት አፈጻጸም ዙሪያ እየመከረ ነው።

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ለምክር ቤት አባላት ባቀረቡት የግማሽ ዓመት አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ባለፉት ስድስት ወራት የትምህርትና የጤና ልማት ሥራዎች አበረታች ውጤት ተመዝግቧል።
የትምህርት ተደራሽነትን በማስፋት ውጤታማነቱን ለማረጋገጥ በክልሉ ከ1ኛ እስከ 12ኛ ክፍል 1ሚሊየን 619 ሺህ ተማሪዎችን መቀበላቸውን ተናግረዋል።
የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥም መጽሐፍት በማባዛት ለአንደኛ እና ለሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች የተማሪ መጽሐፍ ጥምርታን አንድ ለአንድ ማድረስ መቻሉንም አንስተዋል።
በሌላ በኩል በጤና ልማት 587 ሺህ 931 ሴቶች የቤተሰብ ዕቅድ አገልግሎት ተጠቃሚ መሆናቸውን አመልክተዋል።
በግማሽ ዓመቱ የወባ በሽታ ስርጭትን ለመከላከልና ለማከም በተደረገው ጥረት በ491 ሺህ 943 ሰዎች ላይ የወባ ምልክት የታየባቸው በመሆኑ አስፈላጊው ህክምና እንዲያገኙ ተደርጓል።

የክልሉ ምክር ቤት አፌ-ጉባኤ ፀሐይ ወራሳ በበኩላቸው ምክር ቤቱ በሁለንተናዊ የልማት እንቅስቃሴ የህዝቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየሠራ ይገኛል ብለዋል።
የምክር ቤት አባላት ክልሉን ከሙስና በማጽዳት ፈጣን ሁለንተናዊ ልማት እንዲረጋገጥ አበክረው መሥራት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026