
አዲስ አበባ፤ የካቲት 8/2017(ኢዜአ)፦ በሃላፊነት ዘመናቸው በአፍሪካ የሕዝብ የኑሮ ሁኔታ በሚያሻሽሉ ጉዳዮች ላይ ቀዳሚ ትኩረት አድርገው እንደሚሰሩ አዲሱ የአፍሪካ ሕብረት ሊቀ መንበር እና የአንጎላ ፕሬዚዳንት ዣዎ ማኑኤል ጎንሳልቬስ ሎሬንስ ገለጹ።
38ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ ዛሬ መካሄድ የጀመረ ሲሆን ሞሪታኒያ የሕብረቱን ሊቀ መንበርነት ለአንጎላ በይፋ አስረክባለች።

የ2024 የአፍሪካ ሕብረት ሊቀ መንበር የነበሩት የሞሪታኒያ ፕሬዚዳንት መሐመድ ኦውልድ ጋዙዋኒ ለአንጎላ ፕሬዝዳንት ዣዎ ማኑኤል ጎንሳልቬስ ሎሬንስ በ2025 የአፍሪካ ሕብረትን በሊቀ መንበርነት እንዲመሩ አስረክበዋል።
የአንጎላ ፕሬዚዳንት ዣዎ ማኑኤል ጎንሳልቬስ ሎሬንስ እንዳሉት በጉባኤው ለአፍሪካ የሚበጁ ጠቃሚ ውይይቶች ተደርገዋል።
በሊቀመንበርነት ዘመናቸው የበለፀገች አፍሪካን ዕውን ለማድረግ ስራ አጥነት፣ ግጭትን እና ህገ-ወጥ ስደትን ለመቀነስ እንደሚሰሩ ለአብነት ጠቅሰው፤ ዕቅዳቸውን ለማሳካትም የአባል ሀገራት ድጋፍ እንደማይለያቸው ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።
የአፍሪካ 2063 አጀንዳዎችን ከግብ ለማድረስ ለሚደረገው ርብርብ በትኩረት እንደሚሰሩም ገልጽው፤ የህዝብ ኑሮ ለሚያሻሽሉ ተግባራት ቅድሚያ እንደሚሰጡ አንስተዋል።
የሰላም እና የጸጥታ ችግር ያለባቸውን የአህጉሪቱ ሀገራት ወደ ዘላቂ ሰላም እንዲመለሱ እንደሚሰራም አመላክተዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026