የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>በአፍሪካ የሕዝብ ኑሮ ለሚያሻሽሉ ጉዳዮች ቀዳሚ ትኩረት ተሰጥቶ ይሰራል- የአፍሪካ ሕብረት ሊቀ መንበር</p>

Feb 17, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 8/2017(ኢዜአ)፦ በሃላፊነት ዘመናቸው በአፍሪካ የሕዝብ የኑሮ ሁኔታ በሚያሻሽሉ ጉዳዮች ላይ ቀዳሚ ትኩረት አድርገው እንደሚሰሩ አዲሱ የአፍሪካ ሕብረት ሊቀ መንበር እና የአንጎላ ፕሬዚዳንት ዣዎ ማኑኤል ጎንሳልቬስ ሎሬንስ ገለጹ።

38ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ ዛሬ መካሄድ የጀመረ ሲሆን ሞሪታኒያ የሕብረቱን ሊቀ መንበርነት ለአንጎላ በይፋ አስረክባለች።


የ2024 የአፍሪካ ሕብረት ሊቀ መንበር የነበሩት የሞሪታኒያ ፕሬዚዳንት መሐመድ ኦውልድ ጋዙዋኒ ለአንጎላ ፕሬዝዳንት ዣዎ ማኑኤል ጎንሳልቬስ ሎሬንስ በ2025 የአፍሪካ ሕብረትን በሊቀ መንበርነት እንዲመሩ አስረክበዋል።

የአንጎላ ፕሬዚዳንት ዣዎ ማኑኤል ጎንሳልቬስ ሎሬንስ እንዳሉት በጉባኤው ለአፍሪካ የሚበጁ ጠቃሚ ውይይቶች ተደርገዋል።

በሊቀመንበርነት ዘመናቸው የበለፀገች አፍሪካን ዕውን ለማድረግ ስራ አጥነት፣ ግጭትን እና ህገ-ወጥ ስደትን ለመቀነስ እንደሚሰሩ ለአብነት ጠቅሰው፤ ዕቅዳቸውን ለማሳካትም የአባል ሀገራት ድጋፍ እንደማይለያቸው ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።

የአፍሪካ 2063 አጀንዳዎችን ከግብ ለማድረስ ለሚደረገው ርብርብ በትኩረት እንደሚሰሩም ገልጽው፤ የህዝብ ኑሮ ለሚያሻሽሉ ተግባራት ቅድሚያ እንደሚሰጡ አንስተዋል።

የሰላም እና የጸጥታ ችግር ያለባቸውን የአህጉሪቱ ሀገራት ወደ ዘላቂ ሰላም እንዲመለሱ እንደሚሰራም አመላክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026

በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...

Mar 31, 2026