የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>በአፍሪካ የሕዝብ ኑሮ ለሚያሻሽሉ ጉዳዮች ቀዳሚ ትኩረት ተሰጥቶ ይሰራል- የአፍሪካ ሕብረት ሊቀ መንበር</p>

Feb 17, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 8/2017(ኢዜአ)፦ በሃላፊነት ዘመናቸው በአፍሪካ የሕዝብ የኑሮ ሁኔታ በሚያሻሽሉ ጉዳዮች ላይ ቀዳሚ ትኩረት አድርገው እንደሚሰሩ አዲሱ የአፍሪካ ሕብረት ሊቀ መንበር እና የአንጎላ ፕሬዚዳንት ዣዎ ማኑኤል ጎንሳልቬስ ሎሬንስ ገለጹ።

38ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ ዛሬ መካሄድ የጀመረ ሲሆን ሞሪታኒያ የሕብረቱን ሊቀ መንበርነት ለአንጎላ በይፋ አስረክባለች።


የ2024 የአፍሪካ ሕብረት ሊቀ መንበር የነበሩት የሞሪታኒያ ፕሬዚዳንት መሐመድ ኦውልድ ጋዙዋኒ ለአንጎላ ፕሬዝዳንት ዣዎ ማኑኤል ጎንሳልቬስ ሎሬንስ በ2025 የአፍሪካ ሕብረትን በሊቀ መንበርነት እንዲመሩ አስረክበዋል።

የአንጎላ ፕሬዚዳንት ዣዎ ማኑኤል ጎንሳልቬስ ሎሬንስ እንዳሉት በጉባኤው ለአፍሪካ የሚበጁ ጠቃሚ ውይይቶች ተደርገዋል።

በሊቀመንበርነት ዘመናቸው የበለፀገች አፍሪካን ዕውን ለማድረግ ስራ አጥነት፣ ግጭትን እና ህገ-ወጥ ስደትን ለመቀነስ እንደሚሰሩ ለአብነት ጠቅሰው፤ ዕቅዳቸውን ለማሳካትም የአባል ሀገራት ድጋፍ እንደማይለያቸው ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።

የአፍሪካ 2063 አጀንዳዎችን ከግብ ለማድረስ ለሚደረገው ርብርብ በትኩረት እንደሚሰሩም ገልጽው፤ የህዝብ ኑሮ ለሚያሻሽሉ ተግባራት ቅድሚያ እንደሚሰጡ አንስተዋል።

የሰላም እና የጸጥታ ችግር ያለባቸውን የአህጉሪቱ ሀገራት ወደ ዘላቂ ሰላም እንዲመለሱ እንደሚሰራም አመላክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026