የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>በሶማሌ ክልል እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የኢንቨስትመንት ሥራዎች የሀገርን እድገት የሚደግፉ ናቸው</p>

Feb 19, 2025

IDOPRESS

ጅግጅጋ፤የካቲት 11/2017(ኢዜአ)፦በሶማሌ ክልል እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የኢንቨስትመንት ሥራዎች የሀገርን እድገትና ምጣኔ ሃብት የሚደግፉ መሆኑን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) ገለጹ።


የፌዴራል፣የክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የኢንቨስትመንት አስፈጻሚዎች የጋራ የምክክር መድረክ በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ ማካሄዳቸው ይታወሳል።


ከምክክሩ በተጓዳኝ ኮሚሽነሩን ጨምሮ ሌሎች የፌዴራልና የሶማሌ ክልል የስራ ሃላፊዎች በክልሉ እየተከናወኑ ያሉ የኢንቨስትመንት ስራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።


ከጉብኝቱ በኋላ ኢዜአ ያነጋገራቸው የኢትዮጵያ ኢንቨስትመነት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር)፥በክልሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች በስፋት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።


በተለይም ደግሞ የኢንቨስትመንት ልማቱ የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሃብቶች ተሳትፈውበት በሁሉም መስክ በጥሩ አፈፃፀም ላይ መሆኑን ነው ያነሱት።


በዚህም ቀደም ሲል ከውጭ ይገቡ የነበሩ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በማምረት የተጀመሩ ጥረቶችን መደገፍ የሚያስችሉ ተጨባጭ ውጤቶች ተገኝተውበታል ብለዋል።


በዚህ ረገድ የተገኙ ተጨባጭ ውጤቶችን የማሰቀጠልና የማስፋፋት እንዲሁም በዘርፉ ልማት የተሰማሩ ባለሃብተቶችን የመደገፍና ማበረታታት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።


እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የኢንቨስትመንት ሥራዎች የሀገርን እድገትና ምጣኔ ሃብት የሚያግዙና የሚደግፉ መሆናቸውን ገልጸዋል።


በተለይም በከተማው የሚገኘው የስዎይስ ሞተር የመኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ አብዲ ኢብራሂም፤ ፋብሪካው ተሽከርካሪዎችን እየገጣጠመ ለገበያ እያቀረበ መሆኑንና ለ300 ዜጎችም ቋሚ የስራ እድል መፍጠሩን ተናግረዋል።


ሌላው በክልሉ ከተሰማሩ ባለሀብቶች መካከል አቶ መሐመድ ከዲር፤ በ300 ሚሊዮን ብር ካፒታል ያቋቋሙት የታሸገ ውሃ ማምረቻ ፋብሪካ በቀጣይ ሳምንት ስራ የሚጀምር መሆኑን ገልጸዋል።


በዘርፉ ልማት የመንግስት ማበረታቻ ጥሩ መሆኑን ጠቅሰው፥ በቀጣይ ለተሻለ ስኬት የሚሰሩ መሆኑን አረጋግጠዋል።


የሶማሌ ክልል ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ቢሮ ሃላፊ አህመድ ረሺድ፤ በክልሉ በተፈጠረው ምቹ ሁኔታ በዘርፉ የሚሰማሩ ባለሃብቶች ተሳትፎ እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል።


የክልሉ መንግስት ዘርፉን ለማበረታታት የመሬት አቅርቦት፣ መሰረተ ልማቶችን የማሟላትና ሌሎች ድጋፎችን እያደረገ መሆኑንም ገልጸዋል።


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ታኅሣሥ 26 ቀን 2017 ዓ.ም በጅግጅጋ ከተማ ተገኝተው ለሀገር ውስጥ ገበያ የጄቱር መኪናዎች መገጣጠሚያ ፋብሪካን መጎብኘታቸው ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.