የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>ፋይዳ መታወቂያ ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ከፍተኛ ድርሻ አለው</p>

Feb 20, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤የካቲት 12/2017(ኢዜአ)፦ፋይዳ መታወቂያ ተአማኒነትን ለማጎልበትና ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው የኢትዮጵያ ብሔራዊ መታወቂያ አገልግሎት ገለፀ ።


የኢትዮጵያ ብሔራዊ መታወቂያ አገልግሎት ከኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ጋር በመተባበር " ፋይዳ ለኢትዮጵያ " በሚል መሪ ሃሳብ የፓናል ውይይት አካሂዷል።


የኢትዮጵያ ብሄራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ዋና አስተባባሪ አቶ ዮዳሄ አርአያስላሴ፥ ፋይዳ ዜጎች ወጥ ማንነት እንዲኖራቸውና በዛው ልክ የተቀላጠፈ አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል ነው ብለዋል።


አገልግሎቱ ከተቋማት ጋር ትስስር በመፍጠር አሰራራቸውን ለማዘመንና ለማስተሳሰር በትኩረት እየሰራ መሆኑን አብራርተዋል።


የአገልግሎቱ የባለድርሻ አካላት ጉዳይ ዳይሬክተር አቶ ሳሚናስ ሰይፉ ከ 12 ነጥብ 2 ሚሊየን በላይ የሚሆኑ ዜጎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት መሆናቸውን ተናግረዋል።


በቀጣይም የፋይዳ መታወቂያ ምዝገባን በመላው ሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራበት እንደሚገኝ አስታውቀዋል።


የፌዴራል ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ገቢዎች ሚኒስቴር ከፋይዳ ጋር በቅንጅት ከሚሰሩ ተቋማት መካከል ተጠቃሽ ናቸው።


የፌዴራል ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ቶፊቅ ሻፊ፥ ተቋሙ ከህዳር 2017 ዓ.ም ጀምሮ አሰራሩን ከፋይዳ ጋር ማስተሳሰር በመቻሉ ከዚህ ቀደም ሲስተዋሉ የነበሩ ችግሮች ሙሉ በሙሉ መቀረፋቸውን ተናግረዋል።


በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የመርቻንት እና ኤጀንት ማኔጅመንት ዳይሬክተር አቶ ብሌን ሀይለሚካኤል፥ የደንበኞቻችንን ማንነት በትክክል በማወቅ አካውንት ለመክፈትና የብድር አገልግሎት ለመስጠት ፈይዳ ወሳኝ ነው ብለዋል፡፡


በገቢዎች ሚኒስቴር የግብር ከፋዮችና ምዝገባ አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ ደረጀ ፋና፥ ተቋማቸው ከአገልግሎቱ ጋር ትስስር በመፍጠር የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ሙሉ በሙሉ በዲጂታል የታገዙ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን አብራርተዋል፡፡


በሀገር አቀፍ ደረጃ ከአንድ ሺህ በላይ የፋይዳ ምዝገባ ጣቢያዎች ተከፍተው ምዝገባ በማካሄድ ላይ እንደሚገኙ ከተቋሙ የተገኘው መረጃ ያሳያል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026

በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...

Mar 31, 2026