የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>ፋይዳ መታወቂያ ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ከፍተኛ ድርሻ አለው</p>

Feb 20, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤የካቲት 12/2017(ኢዜአ)፦ፋይዳ መታወቂያ ተአማኒነትን ለማጎልበትና ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው የኢትዮጵያ ብሔራዊ መታወቂያ አገልግሎት ገለፀ ።


የኢትዮጵያ ብሔራዊ መታወቂያ አገልግሎት ከኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ጋር በመተባበር " ፋይዳ ለኢትዮጵያ " በሚል መሪ ሃሳብ የፓናል ውይይት አካሂዷል።


የኢትዮጵያ ብሄራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ዋና አስተባባሪ አቶ ዮዳሄ አርአያስላሴ፥ ፋይዳ ዜጎች ወጥ ማንነት እንዲኖራቸውና በዛው ልክ የተቀላጠፈ አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል ነው ብለዋል።


አገልግሎቱ ከተቋማት ጋር ትስስር በመፍጠር አሰራራቸውን ለማዘመንና ለማስተሳሰር በትኩረት እየሰራ መሆኑን አብራርተዋል።


የአገልግሎቱ የባለድርሻ አካላት ጉዳይ ዳይሬክተር አቶ ሳሚናስ ሰይፉ ከ 12 ነጥብ 2 ሚሊየን በላይ የሚሆኑ ዜጎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት መሆናቸውን ተናግረዋል።


በቀጣይም የፋይዳ መታወቂያ ምዝገባን በመላው ሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራበት እንደሚገኝ አስታውቀዋል።


የፌዴራል ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ገቢዎች ሚኒስቴር ከፋይዳ ጋር በቅንጅት ከሚሰሩ ተቋማት መካከል ተጠቃሽ ናቸው።


የፌዴራል ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ቶፊቅ ሻፊ፥ ተቋሙ ከህዳር 2017 ዓ.ም ጀምሮ አሰራሩን ከፋይዳ ጋር ማስተሳሰር በመቻሉ ከዚህ ቀደም ሲስተዋሉ የነበሩ ችግሮች ሙሉ በሙሉ መቀረፋቸውን ተናግረዋል።


በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የመርቻንት እና ኤጀንት ማኔጅመንት ዳይሬክተር አቶ ብሌን ሀይለሚካኤል፥ የደንበኞቻችንን ማንነት በትክክል በማወቅ አካውንት ለመክፈትና የብድር አገልግሎት ለመስጠት ፈይዳ ወሳኝ ነው ብለዋል፡፡


በገቢዎች ሚኒስቴር የግብር ከፋዮችና ምዝገባ አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ ደረጀ ፋና፥ ተቋማቸው ከአገልግሎቱ ጋር ትስስር በመፍጠር የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ሙሉ በሙሉ በዲጂታል የታገዙ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን አብራርተዋል፡፡


በሀገር አቀፍ ደረጃ ከአንድ ሺህ በላይ የፋይዳ ምዝገባ ጣቢያዎች ተከፍተው ምዝገባ በማካሄድ ላይ እንደሚገኙ ከተቋሙ የተገኘው መረጃ ያሳያል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026