
አዲስ አበባ፤ የካቲት 12/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያንና የሩሲያን ታሪካዊ ግንኙነት በንግድና ኢንቨስትመንት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ሁለቱ አገራት በትብብር እንደሚሰሩ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር ተናገሩ።
አፈ-ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር ከሩሲያ ፌዴሬሽን ፌዴራል ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ቫለንቲና ማትቬዬንኮ ጋር ዛሬ ተወያይተዋል።
ውይይቱን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙኃን ማብራሪያ የሰጡት አፈ-ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር በሩሲያና በኢትዮጵያ መካከል ዘመናትን የተሻገረ ጠንካራ ግንኙነት መኖሩን አንስተዋል።
በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ግንኙነት ይበልጥ ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ በአፈ-ጉባኤ ቫለንቲና ከተመራው ልዑክ ጋር ምክክር መደረጉን ተናግረዋል።
በኢንቨስትመንት፣ በቴክኖሎጂ፣ በጤና፣ በኃይል ዘርፍ፣ በኢንፎርሜሽን ደህንነት እና በመገናኛ ቴክኖሎጂ መስክ ያለውን ትብብር ማጠናከር ላይ ያተኮረ ውይይት መደረጉን አብራርተዋል።
በኢትዮጵያና በሩሲያ መካከል የተጀመረው ፓርላሜንታዊ ትብብር ወደ ላቀ ምዕራፍ መሸጋገሩንም ጠቅሰዋል፡፡
የሀገራቱን ግንኙነት ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይም መግባባት ላይ መደረሱን አፈ-ጉባኤ አገኘሁ አስታውቀዋል።
የኢትዮጵያና የሩሲያን ታሪካዊ ግንኙነት በንግድና ኢንቨስትመንት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችል ውይይት መደረጉን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሩሲያ በረራ እያደረገ መሆኑን ገልጸው ይህም ሰዎችና ምርቶችን ለማጓጓዝ ምቹ አጋጣሚ መፍጠሩን አስረድተዋል።
የሁለቱን አገራት የንግድ እና የንግድ ዘርፍ ማህበራትን ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ሥራዎች በቀጣይ እንደሚከናወኑ ተናግረዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026