የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>የዩናይትድ ኪንግደም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አንጄላ ራይነር የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጎበኙ</p>

Feb 20, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፣የካቲት 12/2017 (ኢዜአ)፦የዩናይትድ ኪንግደም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አንጄላ ራይነር የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጎብኝተዋል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሯ እና ልዑካቸው በኢትዮጵያ አየር መንገድ ባደረጉት ጉብኝት፤ የኢትዮጵያ የአቪዬሽን ዩኒቨርሲቲ፣ የአውሮፕላን ጥገና ክፍል እና የተግባራዊ በረራ ማሰልጠኛ ምስለ በረራዎችን መመልከታቸውን የአየር መንገዱ መረጃ ያመለክታል።


በወቅቱ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው እና ከኢትዮጵያ አየር መንገድ አመራር አባላት ጋር ውይይት አካሂደዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዘመናዊ አውሮፕላኖቹ ወደ ዩናይትድ ኪንግደም ለንደን ሂትሮው፣ ለንደን ጋትዊክ እና ማንቼስተር ከተሞች 16 ሳምንታዊ በረራ በማድረግ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ባህላዊ ትስስርን ለማጠናከር እየሰራ ይገኛል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.