የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>በመንግስት እና የግል አጋርነት ከሚለሙ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶቹ እስከ 750 ሜጋ ዋት ኃይል ለማግኘት ታቅዷል - የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል</p>

Feb 21, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2017(ኢዜአ)፡- በመንግስት እና የግል አጋርነት ከሚለሙ ስምንት የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች እስከ 750 ሜጋ ዋት ኃይል ለማግኘት መታቀዱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ።

የተቋሙ የመንግሥት እና የግል አጋርነት መምሪያ የፀሐይና ንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ሥራ አስኪያጅ አቶ አሸናፊ ዘውዴ እንደገለጹት የኃይል ስብጥርን ለማሳደግ እና የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን ለማስፋት በኃይል ማመንጨት ዘርፍ የግል አልሚዎች እንዲሳተፉ የሚያስችል የሕግ ማዕቀፍ ተዘጋጅቷል።

እየተተገበረ ያለው የኢኮኖሚ ማሻሻያ ፖሊሲ የውጭ ምንዛሬ አካውንት ለመክፈት አስቻይ ሁኔታ መፍጠሩን ጠቁመው ፕሮጀክቶቹን ወደ ትግበራ ለማስገባት እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

በዚህም በመንግስትና በግል አጋርነት የሚለሙ ስምንት የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች መለየታቸውን ጠቁመዋል።

የጋድ 1 እና 2፣ ዲቼቶ እና ወራንሶ(የአራት ፕሮጀክቶች) ጥናታቸው መጠናቀቁንም አቶ አሸናፊ ገልጸዋል።

የጋድ 2 እና ወራንሶ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን በመንግስት እና በግል አጋርነት ለማልማት ጨረታ መውጣቱንም ተናግረዋል።

ሁለቱ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች 225 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም እንዳላቸውና ፕሮጀክቶቹን ለማጠናቀቅ 200 ሚሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል።

ፕሮጀክቶቹ በመንግስትና የግል አጋርነት መልማታቸው በተሻለ ጥራትና ጊዜ ለማጠናቀቅ ዕድል ይፈጥራል ነው ያሉት።

ከስምንቱ የፀሐይ ኃይል ማመንጫዎች እስከ 750 ሜጋ ዋት ለማመንጨት ዕቅድ መያዙን ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.