የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ የኮምቦልቻ ከተማ የስማርት ሲቲ ፕሮጀክትን ጎበኙ</p>

Feb 25, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፦በኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ የተመራ የስራ አመራር ልዑክ የኮምቦልቻ ከተማ የስማርት ሲቲ ፕሮጀክት ትግበራን ጎብኝቷል።

በጉብኝቱ ላይ የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ መሀመድ አሚን የሱፍ ተገኝተዋል።

ኩባንያው እና የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር የሚያከናውኑት የስማርት ሲቲ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ምዕራፍ በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ መሆኑ ተገልጿል።

ቀሪ ስራዎችም በአፋጣኝ ተጠናቀው ወደ ስራ እንዲገቡ አቅጣጫ መቀመጡን ከኢትዮ ቴሌኮም የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

ፕሮጀክቱ ኮምቦልቻን ለኢንዱስትሪና ለተለያዩ ኢንቨስትመንቶች ይበልጥ ተመራጭ በማድረግ ተወዳዳሪነቷን የሚያሳድግ እና ለነዋሪዎቿ ምቹ እና ደህንነቱ የተጠበቀ ከተማ እንድትሆን ያደርጋታል ነው የተባለው።

የስማርት ሲቲ ፕሮጀክቱ የመስተዳድሩን አገልግሎቶች፣የግብር አሰባሰብ፣ የትራንስፖርት እና ሌሎች ክፍያዎችን በቴሌብር በማቀላጠፍ የዜጎችን ጊዜና ገንዘብ እንደሚቆጥብም እንዲሁ።

የአሰራር ቅልጥፍናንና ተደራሽነትን በመጨመር ረገድ አስተዋጽኦ እንደሚያበርክት ተነግሯል።

ልዑኩ በከተማዋ የሚገኝ የአረንጓዴ ልማት ፓርክ መጎበኝቱን ከኢትዮ ቴሌኮም የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.