
አዲስ አበባ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፦በኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ የተመራ የስራ አመራር ልዑክ የኮምቦልቻ ከተማ የስማርት ሲቲ ፕሮጀክት ትግበራን ጎብኝቷል።
በጉብኝቱ ላይ የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ መሀመድ አሚን የሱፍ ተገኝተዋል።
ኩባንያው እና የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር የሚያከናውኑት የስማርት ሲቲ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ምዕራፍ በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ መሆኑ ተገልጿል።
ቀሪ ስራዎችም በአፋጣኝ ተጠናቀው ወደ ስራ እንዲገቡ አቅጣጫ መቀመጡን ከኢትዮ ቴሌኮም የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ፕሮጀክቱ ኮምቦልቻን ለኢንዱስትሪና ለተለያዩ ኢንቨስትመንቶች ይበልጥ ተመራጭ በማድረግ ተወዳዳሪነቷን የሚያሳድግ እና ለነዋሪዎቿ ምቹ እና ደህንነቱ የተጠበቀ ከተማ እንድትሆን ያደርጋታል ነው የተባለው።
የስማርት ሲቲ ፕሮጀክቱ የመስተዳድሩን አገልግሎቶች፣የግብር አሰባሰብ፣ የትራንስፖርት እና ሌሎች ክፍያዎችን በቴሌብር በማቀላጠፍ የዜጎችን ጊዜና ገንዘብ እንደሚቆጥብም እንዲሁ።
የአሰራር ቅልጥፍናንና ተደራሽነትን በመጨመር ረገድ አስተዋጽኦ እንደሚያበርክት ተነግሯል።
ልዑኩ በከተማዋ የሚገኝ የአረንጓዴ ልማት ፓርክ መጎበኝቱን ከኢትዮ ቴሌኮም የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026