
አዲስ አበባ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፦በኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ የተመራ የስራ አመራር ልዑክ የኮምቦልቻ ከተማ የስማርት ሲቲ ፕሮጀክት ትግበራን ጎብኝቷል።
በጉብኝቱ ላይ የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ መሀመድ አሚን የሱፍ ተገኝተዋል።
ኩባንያው እና የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር የሚያከናውኑት የስማርት ሲቲ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ምዕራፍ በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ መሆኑ ተገልጿል።
ቀሪ ስራዎችም በአፋጣኝ ተጠናቀው ወደ ስራ እንዲገቡ አቅጣጫ መቀመጡን ከኢትዮ ቴሌኮም የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ፕሮጀክቱ ኮምቦልቻን ለኢንዱስትሪና ለተለያዩ ኢንቨስትመንቶች ይበልጥ ተመራጭ በማድረግ ተወዳዳሪነቷን የሚያሳድግ እና ለነዋሪዎቿ ምቹ እና ደህንነቱ የተጠበቀ ከተማ እንድትሆን ያደርጋታል ነው የተባለው።
የስማርት ሲቲ ፕሮጀክቱ የመስተዳድሩን አገልግሎቶች፣የግብር አሰባሰብ፣ የትራንስፖርት እና ሌሎች ክፍያዎችን በቴሌብር በማቀላጠፍ የዜጎችን ጊዜና ገንዘብ እንደሚቆጥብም እንዲሁ።
የአሰራር ቅልጥፍናንና ተደራሽነትን በመጨመር ረገድ አስተዋጽኦ እንደሚያበርክት ተነግሯል።
ልዑኩ በከተማዋ የሚገኝ የአረንጓዴ ልማት ፓርክ መጎበኝቱን ከኢትዮ ቴሌኮም የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026