የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>ኢትዮጵያ እና ፓኪስታን የንግድ እና ኢንቨስትመንት ትብብራቸውን ለማጠናከር እንደሚሰሩ አስታወቁ</p>

Feb 26, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤የካቲት 18/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ እና ፓኪስታን የንግድ እና ኢንቨስትመንት የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ለማጠናከር እንደሚሰሩ አስታወቁ።

የኢትዮ-ፓኪስታን የቢዝነስ ፎረም በላሆር ከተማ ዛሬ ተካሄዷል።

ፎረሙ በፓኪስታን የኢትዮጵያ ኤምባሲ እና በፓኪስታን የንግድ ሚኒስቴር ትብብር የተዘጋጀ ነው።

በፓኪስታን የኢትዮጵያ አምባሳደር ጀማል በከር በፎረሙ ላይ ለተሳተፉ የፓኪስታን የንግድ ማህበረሰብ አባላት ኢትዮጵያ ያደረገቻቸው የኢኮኖሚ ሪፎርሞች በሀገሪቷ የፈጠረውን የንግድ እና ኢንቨስትመንት ምቹነት አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል።

በግብርና እና ግብርና ማቀነባበሪያ፣ ማኑፋክቸሪንግ፣ ማዕድን ቱሪዝም እና ኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ሰፊ እድሎች እንዳሉ አመልክተዋል።

የአማራጭ ኃይል አቅርቦት፣ የህዝብ ቁጥር ብዛት፣ የሰለጠነ የሰው ኃይል እና አፍሪካን እርስ በእርስ እና ከተቀረው ዓለም ጋር የሚያስተሳስረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለፓኪስታን ባለሀብቶች ኢንቨስትመት ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥር ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ የአፍሪካ ነጻ ንግድ ቀጣና አባል ሀገር መሆኗ እና በአህጉሪቷ ግዙፉን አየር መንገድ መያዟ ተመራጭ የኢንቨስትመንት መዳረሻ ያደርጋታል ነው ያሉት አምባሳደሩ።

አምባሳደሩ የፓኪስታን ባለሀብቶች በአዲስ አበባ በሚዘጋጀው የኢትዮጵያን ምርቶች እና አገልግሎት የሚያስተዋውቅ አውደ ርዕይ (Single Country Exhibition) ተሳትፎ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

አውደ ርዕዩ የኢትዮጵያ እና የፓኪስታን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር እንደሚያስችል ገልጸዋል።


የፓኪስታን የንግድ ልማት ባለስልጣን ዳይሬክተር ጀነራል አብዱል ከሪም ሜሞን ኢትዮጵያ በዓለም ላይ ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት እያስመዘገቡ ካሉ ሀገራት መካከል እንደምትጠቀስ ገልጸዋል።

የፓኪስታን ባለሀብቶች የኢትዮጵያን የንግድ እና ኢንቨስትመንት እድሎች ለመመልከት ፍላጎት እንዳላቸው አመልክተዋል።

ባለሀብቶች የኢትዮጵያን ምርቶች እና አገልግሎት የሚያስተዋውቅ አውደ ርዕይ ላይ እንዲሳተፉ ጥሪ ማቅረባቸውን በፓኪስታን የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026

በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...

Mar 31, 2026