
አዲስ አበባ ፤የካቲት 18/2017(ኢዜአ)፦ የሙያ ብቃት ምዘና ሥርዓቱን ለማሻሻል የተጀመረው ሥራ በፍጥነት ወደ ተግባር ሊገባ እንደሚገባ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለፁ።
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የዘርፎች አፈፃፀም ግምገማ ተካሂዷል፡፡
በመድረኩ የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ አፈፃፀም በመጀመሪያ ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በመድረኩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፣ በሪፎርሙ የተቀመጡ አቅጣጫዎችን ወደ ተግባር ለመቀየር የተደረገው ጥረት አበረታች
ነው፡፡
በዘርፉ የሚሰጠው ስልጠና የሥራ ገበያውን ፍላጎት የሚመልስ መሆኑን ማረጋገጥ እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡
የስልጠናውን ጥራትና አግባብነት ለማረጋገጥ የተጀመረውን ሥራ አጠናክሮ መቀጠል አስፈላጊ ነው ያሉት ሚኒስትሯ የሙያ ብቃት ምዘና ሥርዓቱን ለማሻሻል የተጀመረው ሥራ በፍጥነት ወደ ተግባር መግባት እንዳለበትም አሳስበዋል፡፡
በገጠር ሥራ ዕድል ፈጠራ ግብዓትና ግብይት ላይ ያተኮረ የሙያ ደረጃና ስርዓተ ስልጠና ዝግጅት፣ ተቋማትን በአንፃራዊ የመልማት ፀጋ ለማደራጀት የተጀመረውን ሥራ ወደ ላቀ ደረጃ ማሸጋገር፣ የማሰልጠኛ ተቋማት ኢንተርፕራይዝ ሥራ የገበያ ክፍተቱን በሚሞላ መልኩ ተግባራዊ ማድረግ እንዲሁም ለውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ስልጠና የሚሰጡ ተቋማት በሚፈለገው ደረጃና ጥራት እንዲያከናውኑ ድጋፍና ክትትል ማድረግ የዘርፉ የቀጣይ ወራት ትኩረት እንደሆኑ መገለፁን ከሚኒስቴሩ የተገኘ መረጃ ያመለክታል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026