የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>የሙያ ብቃት ምዘና ሥርዓቱን ለማሻሻል የተጀመረው ሥራ በፍጥነት ወደ ተግባር ሊገባ ይገባል</p>

Feb 26, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ ፤የካቲት 18/2017(ኢዜአ)፦ የሙያ ብቃት ምዘና ሥርዓቱን ለማሻሻል የተጀመረው ሥራ በፍጥነት ወደ ተግባር ሊገባ እንደሚገባ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለፁ።

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የዘርፎች አፈፃፀም ግምገማ ተካሂዷል፡፡

በመድረኩ የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ አፈፃፀም በመጀመሪያ ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡

የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በመድረኩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፣ በሪፎርሙ የተቀመጡ አቅጣጫዎችን ወደ ተግባር ለመቀየር የተደረገው ጥረት አበረታች


ነው፡፡

በዘርፉ የሚሰጠው ስልጠና የሥራ ገበያውን ፍላጎት የሚመልስ መሆኑን ማረጋገጥ እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡


የስልጠናውን ጥራትና አግባብነት ለማረጋገጥ የተጀመረውን ሥራ አጠናክሮ መቀጠል አስፈላጊ ነው ያሉት ሚኒስትሯ የሙያ ብቃት ምዘና ሥርዓቱን ለማሻሻል የተጀመረው ሥራ በፍጥነት ወደ ተግባር መግባት እንዳለበትም አሳስበዋል፡፡

በገጠር ሥራ ዕድል ፈጠራ ግብዓትና ግብይት ላይ ያተኮረ የሙያ ደረጃና ስርዓተ ስልጠና ዝግጅት፣ ተቋማትን በአንፃራዊ የመልማት ፀጋ ለማደራጀት የተጀመረውን ሥራ ወደ ላቀ ደረጃ ማሸጋገር፣ የማሰልጠኛ ተቋማት ኢንተርፕራይዝ ሥራ የገበያ ክፍተቱን በሚሞላ መልኩ ተግባራዊ ማድረግ እንዲሁም ለውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ስልጠና የሚሰጡ ተቋማት በሚፈለገው ደረጃና ጥራት እንዲያከናውኑ ድጋፍና ክትትል ማድረግ የዘርፉ የቀጣይ ወራት ትኩረት እንደሆኑ መገለፁን ከሚኒስቴሩ የተገኘ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.