
ዲላ፤ የካቲት 19/2017 (ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልሉ የግብርና ልማት ተግዳሮቶችን በመፍታት ምርታማነትን ለማሳደግ መረባረብ እንደሚገባ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ አሳሰቡ።
"የግብርና ምርታማነት ለብልፅግናችን" በሚል መሪ ቃል የክልሉ የ2017 ዓ.ም የበልግ አዝመራ ተግባራት ማስጀመሪያ ንቅናቄ መድረክ ዛሬ በጌዴኦ ዞን ዲላ ከተማ እየተካሄደ ነው።

ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ እንዳሉት ባለፉት ዓመታት በክልሉ ምርታማነትን ለማሳደግ በተደረገ ጥረት ውጤት ተመዝግቧል።
ይሁንና የአየር ንብረት ለውጥ፣ የተባይና የአረም ቁጥጥር፣ የቴክኖሎጂ አጠቀቀም ውስንነት እንዲሁም የድህረ ምርት አያያዝና የገበያ ትስስር በክልሉ የግብርና ልማት ፈተናዎች መሆናቸውን አስረድተዋል።
እነዚህን የግብርና ልማት ተግዳሮቶች በመፍታት የበልግ እርሻ ምርታማነትን ለማሳደግ ባለድርሻ አካላት በርብርብ ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል።
በተለይ ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጂነት ለመውጣት በሚደረገው ጥረት በየደረጃው ያለው አመራርና ባለሙያ የልማት አርበኛ መሆን እንዳለበት አስገንዝበዋል።
በምክትል ርእሰ መስተዳደር ማዕረግ የግብርናና ገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ሃላፊ መሪሁን ፍቅሩ (ዶ/ር) በበኩላቸው ክልሉ በሀገር ደረጃ ያለውን የምርት ድርሻ ለማሳደግ ለበልግ አዝመራ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል ብለዋል።
በተለይ የሜካናይዝድ እና የኩታ ገጠም እርሻ ልማትን ከማጠናከር ባለፈ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሻሻል ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ አስታውቀዋል።
በዚህም በተያዘው የበልግ እርሻ በክልሉ ከ848 ሺህ 155 ሄክታር በላይ መሬት በማረስ ከ77 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት ታቅዷል ብለዋል።
ለዕቅዱ ስኬታማነት የምርምር ተቋማት፣ የግብርና ሴክተርና ባለድርሻ አካት በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ ቢሮ ሀላፊው አሳስበዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026