
ዲላ፤ የካቲት 19/2017 (ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልሉ የግብርና ልማት ተግዳሮቶችን በመፍታት ምርታማነትን ለማሳደግ መረባረብ እንደሚገባ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ አሳሰቡ።
"የግብርና ምርታማነት ለብልፅግናችን" በሚል መሪ ቃል የክልሉ የ2017 ዓ.ም የበልግ አዝመራ ተግባራት ማስጀመሪያ ንቅናቄ መድረክ ዛሬ በጌዴኦ ዞን ዲላ ከተማ እየተካሄደ ነው።

ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ እንዳሉት ባለፉት ዓመታት በክልሉ ምርታማነትን ለማሳደግ በተደረገ ጥረት ውጤት ተመዝግቧል።
ይሁንና የአየር ንብረት ለውጥ፣ የተባይና የአረም ቁጥጥር፣ የቴክኖሎጂ አጠቀቀም ውስንነት እንዲሁም የድህረ ምርት አያያዝና የገበያ ትስስር በክልሉ የግብርና ልማት ፈተናዎች መሆናቸውን አስረድተዋል።
እነዚህን የግብርና ልማት ተግዳሮቶች በመፍታት የበልግ እርሻ ምርታማነትን ለማሳደግ ባለድርሻ አካላት በርብርብ ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል።
በተለይ ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጂነት ለመውጣት በሚደረገው ጥረት በየደረጃው ያለው አመራርና ባለሙያ የልማት አርበኛ መሆን እንዳለበት አስገንዝበዋል።
በምክትል ርእሰ መስተዳደር ማዕረግ የግብርናና ገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ሃላፊ መሪሁን ፍቅሩ (ዶ/ር) በበኩላቸው ክልሉ በሀገር ደረጃ ያለውን የምርት ድርሻ ለማሳደግ ለበልግ አዝመራ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል ብለዋል።
በተለይ የሜካናይዝድ እና የኩታ ገጠም እርሻ ልማትን ከማጠናከር ባለፈ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሻሻል ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ አስታውቀዋል።
በዚህም በተያዘው የበልግ እርሻ በክልሉ ከ848 ሺህ 155 ሄክታር በላይ መሬት በማረስ ከ77 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት ታቅዷል ብለዋል።
ለዕቅዱ ስኬታማነት የምርምር ተቋማት፣ የግብርና ሴክተርና ባለድርሻ አካት በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ ቢሮ ሀላፊው አሳስበዋል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026