
ቁሊቶ፤ የካቲት 19/2017(ኢዜአ):- በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጠንካራ የሕብረት ስራ ማህበራትን በማደራጀት የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታውቋል፡፡
በሀላባ ዞን "የተዋሃዱ ህብረት ስራ ዩኒየኖች ለሁለንተናዊ ብልፅግና "በሚል መሪ ሀሳብ የዩኒየኖች የውህደት መድረክ ተካሂዷል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ዑስማን ስሩር በወቅቱ እንዳሉት መንግስት የህብረት ስራ ማህበራት አደረጃጀቶችን በማጠናከር ከሀገር አልፎ በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ለማስቻል የሪፎርም ስራ በማከናወን ላይ ይገኛል ብለዋል፡፡
የክልሉ ህብረት ስራ ማህበራት የሚጠበቅባቸውን ውጤት ከማስመዝገብ አኳያ በርካታ ጉድለቶች ያለባቸው መሆኑን ተከትሎ በአዲስ መልክ ሪፎርም ማድረግ ማስፈለጉንም ጠቁመዋል፡
ግብርናን በማዘመን ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ፣ በግብይት ስርዓት ውስጥ የሚስተዋለውን ችግር በመፍታትና የማህበረሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳላቸው አስረድተዋል፡፡
በክልሉ ጠንካራ የህብረት ስራ ማህበራትን በማደራጀት የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራም ገልፀዋል፡፡
በመርሐ ግብሩ ላይም የክልሉ ህብረት ስራ ኤጀንሲ ኃላፊ አቶ ተመስገን ጎዴቦን ጨምሮ የዞኑ እና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና የህብረት ስራ ማህበራት አመራሮች እየተሳተፉ ነው፡፡
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026