
ቁሊቶ፤ የካቲት 19/2017(ኢዜአ):- በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጠንካራ የሕብረት ስራ ማህበራትን በማደራጀት የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታውቋል፡፡
በሀላባ ዞን "የተዋሃዱ ህብረት ስራ ዩኒየኖች ለሁለንተናዊ ብልፅግና "በሚል መሪ ሀሳብ የዩኒየኖች የውህደት መድረክ ተካሂዷል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ዑስማን ስሩር በወቅቱ እንዳሉት መንግስት የህብረት ስራ ማህበራት አደረጃጀቶችን በማጠናከር ከሀገር አልፎ በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ለማስቻል የሪፎርም ስራ በማከናወን ላይ ይገኛል ብለዋል፡፡
የክልሉ ህብረት ስራ ማህበራት የሚጠበቅባቸውን ውጤት ከማስመዝገብ አኳያ በርካታ ጉድለቶች ያለባቸው መሆኑን ተከትሎ በአዲስ መልክ ሪፎርም ማድረግ ማስፈለጉንም ጠቁመዋል፡
ግብርናን በማዘመን ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ፣ በግብይት ስርዓት ውስጥ የሚስተዋለውን ችግር በመፍታትና የማህበረሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳላቸው አስረድተዋል፡፡
በክልሉ ጠንካራ የህብረት ስራ ማህበራትን በማደራጀት የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራም ገልፀዋል፡፡
በመርሐ ግብሩ ላይም የክልሉ ህብረት ስራ ኤጀንሲ ኃላፊ አቶ ተመስገን ጎዴቦን ጨምሮ የዞኑ እና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና የህብረት ስራ ማህበራት አመራሮች እየተሳተፉ ነው፡፡
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026