
ቁሊቶ፤ የካቲት 19/2017(ኢዜአ):- በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጠንካራ የሕብረት ስራ ማህበራትን በማደራጀት የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታውቋል፡፡
በሀላባ ዞን "የተዋሃዱ ህብረት ስራ ዩኒየኖች ለሁለንተናዊ ብልፅግና "በሚል መሪ ሀሳብ የዩኒየኖች የውህደት መድረክ ተካሂዷል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ዑስማን ስሩር በወቅቱ እንዳሉት መንግስት የህብረት ስራ ማህበራት አደረጃጀቶችን በማጠናከር ከሀገር አልፎ በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ለማስቻል የሪፎርም ስራ በማከናወን ላይ ይገኛል ብለዋል፡፡
የክልሉ ህብረት ስራ ማህበራት የሚጠበቅባቸውን ውጤት ከማስመዝገብ አኳያ በርካታ ጉድለቶች ያለባቸው መሆኑን ተከትሎ በአዲስ መልክ ሪፎርም ማድረግ ማስፈለጉንም ጠቁመዋል፡
ግብርናን በማዘመን ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ፣ በግብይት ስርዓት ውስጥ የሚስተዋለውን ችግር በመፍታትና የማህበረሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳላቸው አስረድተዋል፡፡
በክልሉ ጠንካራ የህብረት ስራ ማህበራትን በማደራጀት የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራም ገልፀዋል፡፡
በመርሐ ግብሩ ላይም የክልሉ ህብረት ስራ ኤጀንሲ ኃላፊ አቶ ተመስገን ጎዴቦን ጨምሮ የዞኑ እና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና የህብረት ስራ ማህበራት አመራሮች እየተሳተፉ ነው፡፡
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026