የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>የጎንደር ከተማ የስራ ሀላፊዎች በጅማ ከተማ የልማት ስራዎች የልምድ ልውውጥ አደረጉ</p>

Feb 28, 2025

IDOPRESS

ጅማ፣የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦የጎንደር ከተማ የስራ ሀላፊች በጅማ ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎች የልምድ ልውውጥ አደረጉ።

በጎንደር ከተማ ከንቲባ በአቶ ቻላቸው ዳኘው የተመራ የስራ ኃላፊዎች ቡድን የጅማ ከተማን የኮሪደርና ልማትና ሌሎች የከተማ ግብርና ስራዎችን እየጎበኙ ነው።

ከንቲባው በወቅቱ እንዳሉት፥ በጅማ ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የኮሪደር ልማት፣የከተማ የግብርና እንዲሁም የሴፍቲኔት እንቅስቃሴ ለሌሎች ከተሞችም ትልቅ ተሞክሮ የሚሆን ነው።

ሁለቱ ከተሞች በኢትዮጵያ ካሉ ጥንታዊ ታሪክ ያላቸው ከተሞች መካከል መሆናቸውን ጠቅሰው፥ በጅማ ከተማ ያደረጉት ጉብኝትም የከተማ ልማት ስራ ልምድን ለመለዋወጥ እና ለእርስ በርስ ትስስር የሚያግዝ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በተለይም በጅማ ከተማ የኮሪደር እና የአረንጓዴ ስፍራዎች ልማት ለሌሎች ከተሞችም መልካም ተሞክሮ መሆን የሚችል ነው ብለዋል።

የጅማ ህዝብ የልማቱ ባለቤት በመሆንና የአመራሩ ቁርጠኝነት የሚደነቅ መሆኑን መገንዘባቸውን ተናግረዋል።

በከተማዋ የንብ ማነብ ስራን ለማዘመን የዘመናዊ ቀፎ ተደራሽነት፣ የቆሻሻ ማስወገጃና መልሶ በመጠቀም ለተፈጥሮ ማዳበሪያነት ለማዋል የሚያስችል ፕሮጀክት እና የኮሪደር ልማቱ ልዩ ተሞክሮ የሚሆን ነው ሲሉም አክለዋል።

የጅማ ከተማ ከንቲባ አቶ ጣሀ ቀመር በበኩላቸው፥ ጉብኝቱ አብሮነትን ለማጎልበትና በተሰሩ የልማት ስራዎች ላይ ልምድን የምንለዋወጥበት ነው ብለዋል።

በጅማ ከተማ የኮሪደር፣የሴፍቲኔት ፕሮግራም፣ የከተማ ግብርናና ሌሎች የልማት ስራዎች በትኩረት እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል።

ጉብኝቱ የሁለቱን ከተሞች ትስስር በይበልጥ ከማጠናከር ባሻገር መልካም የልማት ስራ ልምድ ልውውጥ የሚደረግበት እንደሆነም አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026