
ጅማ፣የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦የጎንደር ከተማ የስራ ሀላፊች በጅማ ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎች የልምድ ልውውጥ አደረጉ።
በጎንደር ከተማ ከንቲባ በአቶ ቻላቸው ዳኘው የተመራ የስራ ኃላፊዎች ቡድን የጅማ ከተማን የኮሪደርና ልማትና ሌሎች የከተማ ግብርና ስራዎችን እየጎበኙ ነው።
ከንቲባው በወቅቱ እንዳሉት፥ በጅማ ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የኮሪደር ልማት፣የከተማ የግብርና እንዲሁም የሴፍቲኔት እንቅስቃሴ ለሌሎች ከተሞችም ትልቅ ተሞክሮ የሚሆን ነው።
ሁለቱ ከተሞች በኢትዮጵያ ካሉ ጥንታዊ ታሪክ ያላቸው ከተሞች መካከል መሆናቸውን ጠቅሰው፥ በጅማ ከተማ ያደረጉት ጉብኝትም የከተማ ልማት ስራ ልምድን ለመለዋወጥ እና ለእርስ በርስ ትስስር የሚያግዝ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በተለይም በጅማ ከተማ የኮሪደር እና የአረንጓዴ ስፍራዎች ልማት ለሌሎች ከተሞችም መልካም ተሞክሮ መሆን የሚችል ነው ብለዋል።
የጅማ ህዝብ የልማቱ ባለቤት በመሆንና የአመራሩ ቁርጠኝነት የሚደነቅ መሆኑን መገንዘባቸውን ተናግረዋል።
በከተማዋ የንብ ማነብ ስራን ለማዘመን የዘመናዊ ቀፎ ተደራሽነት፣ የቆሻሻ ማስወገጃና መልሶ በመጠቀም ለተፈጥሮ ማዳበሪያነት ለማዋል የሚያስችል ፕሮጀክት እና የኮሪደር ልማቱ ልዩ ተሞክሮ የሚሆን ነው ሲሉም አክለዋል።
የጅማ ከተማ ከንቲባ አቶ ጣሀ ቀመር በበኩላቸው፥ ጉብኝቱ አብሮነትን ለማጎልበትና በተሰሩ የልማት ስራዎች ላይ ልምድን የምንለዋወጥበት ነው ብለዋል።
በጅማ ከተማ የኮሪደር፣የሴፍቲኔት ፕሮግራም፣ የከተማ ግብርናና ሌሎች የልማት ስራዎች በትኩረት እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል።
ጉብኝቱ የሁለቱን ከተሞች ትስስር በይበልጥ ከማጠናከር ባሻገር መልካም የልማት ስራ ልምድ ልውውጥ የሚደረግበት እንደሆነም አስታውቀዋል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026