የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>የዲጂታል መሰረተ ልማቶችና ስትራቴጂዎች የኢትዮጵያን የዲጂታል ሽግግር ጉዞ ያፋጥናሉ</p>

Mar 3, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 22/2017(ኢዜአ)፦ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 የተዘረጉ መሰረተ ልማቶች እና የተነደፉ ስትራቴጂዎች የኢትዮጵያን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ የሚያሳኩ መሆናቸውን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ይሹሩን ዓለማየሁ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ ኢትዮጵያን የአፍሪካ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ማዕከል ለማድረግ የተለያዩ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው፡፡

በሀገር ውስጥ የዲጂታል መሰረተ ልማት በመዘርጋት እና ድንበር ተሻጋሪ የኢ-ኮሜርስ ንግድን ማሳለጥ የሚያስችሉ ሥራዎችን እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ኢትዮጵያ የዲጂታል አፍሪካን ዕውን ማድረግ ፖሊሲ አውጭዎች፣ የዘርፉ ባለሙያዎችና መሪዎች ተገናኝተው በጋራ የሚመክሩበት ዓለም አቀፍ መድረክም ታዘጋጃለች ብለዋል፡፡

ከዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ጉዞ የሚያግዙ የኢ-ኮሜርስና የኤሌክትሮኒክ ስትራቴጂዎች ጸድቀው ሥራ ላይ መዋላቸውን ገልጸዋል፡፡

ስታርት አፕ፣ የአምስት ሚሊዬን ኮደርስ ስልጠና የኢትዮጵያን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን የሚያቀላጥፉ አስቻይ ሁኔታዎች መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

እነዚህ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 የተዘረጉ መሰረተ ልማቶች እና የተነደፉ ስትራቴጂዎች የኢትዮጵያን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ የሚያሳኩ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የሰው ሰራሽ አስተውሎት ስትራቴጂ በመንደፍ እና ተቋም በመገንባት ለዘርፉ እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረገች መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ኢትዮጵያ ጠንካራ የሳይበር ደህንነት ተቋም በመገንባት፣ በግሉ ዘርፍ መካከል ጤናማ ውድድር ማድረግ የሚያስችል ሥነ ምህዳር በመፍጠር ከራሷም አልፎ ለአፍሪካውያን ልምድ የሚሆን አቅም ገንብታለች ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.