
ሶዶ፤ የካቲት 24/2017 (ኢዜአ):-በወላይታ ዞን ከ1 ሺህ 200 ሄክታር በሚበልጥ መሬት የበጋ መስኖ ስንዴ እየለማ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።
በዞኑ እየተከናወነ ያለውን የመስኖ ልማትና ሌሎች ተያያዥ የግብርና ሥራዎች በተመለከተ የዞኑ የግብርና መምሪያ ምክትል ኃላፊና የእርሻ ዘርፍ ሃላፊ ታምሩ መለቆ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል።

በማብራሪያቸውም በዞኑ የመስኖ ልማትን ለማጠናከር አርሶ አደሮችን በማደራጀት አስፈላጊውን እገዛና ድጋፍ በማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በዞኑ ለበጋ መስኖ ስንዴ የምርጥ ዘር እና ሌሎች ግብአቶች ቀደም ብለው ተደራሽ መደረጋቸውን አስታውሰው በዚህም 1 ሺህ 233 ሄክታር መሬት በበጋ መስኖ ስንዴ ሰብል መሸፈኑንና 61 ሺህ ኩንታል ምርት ይሰበሰባል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል።

የዱጉና ፋንጎ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊና የእርሻ ዘርፍ `ኃላፊ አሸናፊ ብዙነህ እንደገለጹት፤ በወረዳው 1ሺህ 252 ወጣቶች በማህበር ተደራጅተው የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት እያከናወኑ ይገኛሉ።
በወረዳው ደንዶ ኮይሻ ሁምቦ እና ጨርቻ ቀበሌዎች በማህበር የተደራጁ ወጣቶች በብላቴ ወንዝ ዳር የበጋ መስኖ ስንዴ እያለሙ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በማህበር የተደራጁት 12 ወጣቶች በ40 ሄክታር መሬት ላይ ስንዴ በመስኖ እያለሙ መሆናቸውንና ከልማቱም ጥሩ ውጤት እየጠበቁ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የማህበሩ ሰብሳቢ አስራት ዘውገ ለልማቱ ቀደም ብሎ የአፈር ማዳበሪያና ዘር መቅረቡን አስታውሶ ከዘንድሮው የመስኖ ልማት ከ1 ሺህ 380 ኩንታል በላይ የስንዴ ምርት እንጠብቃለን ብሏል።

የማህበሩ አባል መንግስቱ ሻካ በበኩላቸው በየደረጃው በአመራሩና በባለሙያዎች በተደረገላቸው ድጋፍ በብላቴ ወንዝ ዳርቻ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት እያከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል።
"በልማቱም ጠንክረን በመስራታችን ጥሩ ውጤት እንጠብቃለን ሲሉ" ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026