
ሶዶ፤ የካቲት 24/2017 (ኢዜአ):-በወላይታ ዞን ከ1 ሺህ 200 ሄክታር በሚበልጥ መሬት የበጋ መስኖ ስንዴ እየለማ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።
በዞኑ እየተከናወነ ያለውን የመስኖ ልማትና ሌሎች ተያያዥ የግብርና ሥራዎች በተመለከተ የዞኑ የግብርና መምሪያ ምክትል ኃላፊና የእርሻ ዘርፍ ሃላፊ ታምሩ መለቆ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል።

በማብራሪያቸውም በዞኑ የመስኖ ልማትን ለማጠናከር አርሶ አደሮችን በማደራጀት አስፈላጊውን እገዛና ድጋፍ በማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በዞኑ ለበጋ መስኖ ስንዴ የምርጥ ዘር እና ሌሎች ግብአቶች ቀደም ብለው ተደራሽ መደረጋቸውን አስታውሰው በዚህም 1 ሺህ 233 ሄክታር መሬት በበጋ መስኖ ስንዴ ሰብል መሸፈኑንና 61 ሺህ ኩንታል ምርት ይሰበሰባል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል።

የዱጉና ፋንጎ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊና የእርሻ ዘርፍ `ኃላፊ አሸናፊ ብዙነህ እንደገለጹት፤ በወረዳው 1ሺህ 252 ወጣቶች በማህበር ተደራጅተው የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት እያከናወኑ ይገኛሉ።
በወረዳው ደንዶ ኮይሻ ሁምቦ እና ጨርቻ ቀበሌዎች በማህበር የተደራጁ ወጣቶች በብላቴ ወንዝ ዳር የበጋ መስኖ ስንዴ እያለሙ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በማህበር የተደራጁት 12 ወጣቶች በ40 ሄክታር መሬት ላይ ስንዴ በመስኖ እያለሙ መሆናቸውንና ከልማቱም ጥሩ ውጤት እየጠበቁ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የማህበሩ ሰብሳቢ አስራት ዘውገ ለልማቱ ቀደም ብሎ የአፈር ማዳበሪያና ዘር መቅረቡን አስታውሶ ከዘንድሮው የመስኖ ልማት ከ1 ሺህ 380 ኩንታል በላይ የስንዴ ምርት እንጠብቃለን ብሏል።

የማህበሩ አባል መንግስቱ ሻካ በበኩላቸው በየደረጃው በአመራሩና በባለሙያዎች በተደረገላቸው ድጋፍ በብላቴ ወንዝ ዳርቻ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት እያከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል።
"በልማቱም ጠንክረን በመስራታችን ጥሩ ውጤት እንጠብቃለን ሲሉ" ገልጸዋል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026