የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>በክልሉ የቡና ምርት ጥራትና ምርታማነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው</p>

Mar 4, 2025

IDOPRESS

መቱ፤ የካቲት 24/2017(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ቡና አብቃይ በሆኑ አካባቢዎች ቡናን በጥራትና በብዛት ለማምረት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑ ተገለጸ።

በብልጽግና ፓርቲ ኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነመራ ቡሊን ጨምሮ የክልልና የዞን የስራ አመራር አባላት የመቱ-ጎሬ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታንና በመቱ ወረዳ እየተከናወነ የሚገኘውን የቡና ተክል ዕድሳት ስራን ጎብኝተዋል።

በጉብኝቱ ወቅት ኃላፊው አቶ ነመራ ቡሊ እንዳሉት ከተያዙት የግብርና አቅጣጫዎች ትልቅ ትኩረት ከተሰጣቸው የልማት ተግባራት መካከል ቡና አንዱ ነው።

በክልሉ ቡና አብቃይ በሆኑ አካባቢዎች ቡናን በጥራትና በብዛት ለማምረት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህም አርሶ አደሮችና በቡና ልማት ላይ የተሰማሩ አካላት የቡና ጥራትን ለማስጠበቅ ትልቅ ተኩረት ሊሰጡት እንደሚገባ አስረድተዋል።

በተያያዘ ዜና የስራ ኃላፊዎቹ የመቱ-ጎሬ አየር ማረፊያ የግንባታ ሂደትን የተመለከቱ ሲሆን ግንባታው እየተፋጠነ መሆኑም ተመልክተዋል።

የመቱ-ጎሬ አየር ማረፊያ ግንባታ ፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር አስመላሽ አባይ፤ ግንባታው ከተጀመረ ሁለት ዓመታት ያስቆጠረው ፕሮጀክቱ አሁን ላይ 69 በመቶ መድረሱን ገልጸዋል።

በአንድ ዓመት ውስጥ ግንባታውን ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው ብለዋል።

የኢሉአባቦር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳልካቸው ተፈሪ የመቱ-ጎሬ አውሮፕላን ማረፊያ ሌላ ተጨማሪ የልማት ዕድሎችን ይዞ የሚመጣ መሆኑን አንስተው በቱሪዝም፣ በኢንቨስትመንትና በግብርና ጭምር መነቃቃትን የሚፈጥር እንደሆነ ገልጸዋል።

በኢሉአባቦር ዞን በተያዘው ዓመት በ16 ሺህ ሔክታር መሬት ላይ የቡና ዕድሳት ስራ በጉንደላ እና በንቅለ ተከላ የሚከናወን መሆኑን የገለጹት የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ መልካሙ ጫሊ ናቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.