
መቱ፤ የካቲት 24/2017(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ቡና አብቃይ በሆኑ አካባቢዎች ቡናን በጥራትና በብዛት ለማምረት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑ ተገለጸ።
በብልጽግና ፓርቲ ኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነመራ ቡሊን ጨምሮ የክልልና የዞን የስራ አመራር አባላት የመቱ-ጎሬ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታንና በመቱ ወረዳ እየተከናወነ የሚገኘውን የቡና ተክል ዕድሳት ስራን ጎብኝተዋል።
በጉብኝቱ ወቅት ኃላፊው አቶ ነመራ ቡሊ እንዳሉት ከተያዙት የግብርና አቅጣጫዎች ትልቅ ትኩረት ከተሰጣቸው የልማት ተግባራት መካከል ቡና አንዱ ነው።
በክልሉ ቡና አብቃይ በሆኑ አካባቢዎች ቡናን በጥራትና በብዛት ለማምረት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም አርሶ አደሮችና በቡና ልማት ላይ የተሰማሩ አካላት የቡና ጥራትን ለማስጠበቅ ትልቅ ተኩረት ሊሰጡት እንደሚገባ አስረድተዋል።
በተያያዘ ዜና የስራ ኃላፊዎቹ የመቱ-ጎሬ አየር ማረፊያ የግንባታ ሂደትን የተመለከቱ ሲሆን ግንባታው እየተፋጠነ መሆኑም ተመልክተዋል።
የመቱ-ጎሬ አየር ማረፊያ ግንባታ ፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር አስመላሽ አባይ፤ ግንባታው ከተጀመረ ሁለት ዓመታት ያስቆጠረው ፕሮጀክቱ አሁን ላይ 69 በመቶ መድረሱን ገልጸዋል።
በአንድ ዓመት ውስጥ ግንባታውን ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው ብለዋል።
የኢሉአባቦር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳልካቸው ተፈሪ የመቱ-ጎሬ አውሮፕላን ማረፊያ ሌላ ተጨማሪ የልማት ዕድሎችን ይዞ የሚመጣ መሆኑን አንስተው በቱሪዝም፣ በኢንቨስትመንትና በግብርና ጭምር መነቃቃትን የሚፈጥር እንደሆነ ገልጸዋል።
በኢሉአባቦር ዞን በተያዘው ዓመት በ16 ሺህ ሔክታር መሬት ላይ የቡና ዕድሳት ስራ በጉንደላ እና በንቅለ ተከላ የሚከናወን መሆኑን የገለጹት የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ መልካሙ ጫሊ ናቸው።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026