የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>በቡታጅራ ከተማ የተቋቋሙ ከሰንበት እስከ ሰንበት የግብይት ማዕከላት ገበያን እያረጋጉ ነው---ሸማቾች</p>

Mar 5, 2025

IDOPRESS

ቡታጅራ፤ የካቲት 26/2017 (ኢዜአ)--በቡታጅራ ከተማ የተቋቋሙ ከሰንበት እስከ ሰንበት የግብይት ማዕከላት ገበያን በማረጋጋት በኩል ጉልህ አስተዋጾ እያበረከቱ መሆናቸውን ሸማቾች ገለጹ።

አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡ ሸማቾች መካከል ወይዘሮ ሰላማዊት ታምሩ እደገለጹት፣ ማዕከላቱ አምራቹን ከሸማቹ ጋር በቀጥታ ስለሚያገናኝ የሚፈልጉትን ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ እየገዙ ነው።


ሰው ሰራሽ የምርት አቅርቦት እጥረት እንዲከሰት የሚያደርጉ ህገወጥ ደላሎችን ከግብይት ሥርአቱ እንዲወጡ መደረጉን የምርት አቅርቦቱ እንዲሻሻል ማድረጉንም ተናግረዋል።

የግብይት ማዕከላቱ ምርቶችን በቅርበትና በተመጣጣኝ ዋጋ ለመግዛት እንዳስቻላቸው የጠቀሱት ወይዘሮ ሰላማዊት፣ በተለይ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ዜጎችን ይበልጥ ተጠቃሚ በማድረጋቸው እንዲጠናከሩ ጠይቀዋል።


በከተማው የቀበሌ 02 ነዋሪ ወይዘሮ ሄለን እሸቴ በበኩላቸው የግብይት ማዕከላቱ ገበያው እንዲረጋጋ የራሰቻውን አስተዋጾ ማድረጋቸውን ተናግረዋል።

ማዕከላቱ የራሳቸውን ጥቅም ብቻ በሚያስቡ ነጋዴዎች የሚደረግ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪን ለመቆጣጠር እያስቻሉ መሆናቸውንም ገልጸዋል።

የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አብዱ አህመድ በበኩላቸው አምራቹንና ሸማቹን በቀጥታ የሚያገናኙ ሦስት ከሰንበት እስከ ሰንበት የግብይት ማዕከላት መቋቋማቸውን ገልጸዋል።


በማዕከላቱ አማካኝነት ለማህበረሰቡ ምርት በቀጥታ እየቀረበ መሆኑን ገልጸው፣ ይህም ማህበረሰቡ በአቅሙ የሚፈልገውን እንዲሸምት ዕድል ፈጥሯል ብለዋል።

በቀጣይም ተጨማሪ ማዕከላትን በማስፋፋት ህብረተሰቡን ይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግ እንደሚሰራ ገልፀዋል።

ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ የተገኘው መረጃ እንደሚያሳየው አምራቹንና ነጋዴውን በቀጥታ የሚያገናኙ 134 ከሰንበት እስከ ሰንበት የግብይት ማዕከላት በክልሉ ተቋቁመው አገልግሎት በመስጠት ላይ ናቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.