
ቡታጅራ፤ የካቲት 26/2017 (ኢዜአ)--በቡታጅራ ከተማ የተቋቋሙ ከሰንበት እስከ ሰንበት የግብይት ማዕከላት ገበያን በማረጋጋት በኩል ጉልህ አስተዋጾ እያበረከቱ መሆናቸውን ሸማቾች ገለጹ።
አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡ ሸማቾች መካከል ወይዘሮ ሰላማዊት ታምሩ እደገለጹት፣ ማዕከላቱ አምራቹን ከሸማቹ ጋር በቀጥታ ስለሚያገናኝ የሚፈልጉትን ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ እየገዙ ነው።

ሰው ሰራሽ የምርት አቅርቦት እጥረት እንዲከሰት የሚያደርጉ ህገወጥ ደላሎችን ከግብይት ሥርአቱ እንዲወጡ መደረጉን የምርት አቅርቦቱ እንዲሻሻል ማድረጉንም ተናግረዋል።
የግብይት ማዕከላቱ ምርቶችን በቅርበትና በተመጣጣኝ ዋጋ ለመግዛት እንዳስቻላቸው የጠቀሱት ወይዘሮ ሰላማዊት፣ በተለይ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ዜጎችን ይበልጥ ተጠቃሚ በማድረጋቸው እንዲጠናከሩ ጠይቀዋል።

በከተማው የቀበሌ 02 ነዋሪ ወይዘሮ ሄለን እሸቴ በበኩላቸው የግብይት ማዕከላቱ ገበያው እንዲረጋጋ የራሰቻውን አስተዋጾ ማድረጋቸውን ተናግረዋል።
ማዕከላቱ የራሳቸውን ጥቅም ብቻ በሚያስቡ ነጋዴዎች የሚደረግ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪን ለመቆጣጠር እያስቻሉ መሆናቸውንም ገልጸዋል።
የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አብዱ አህመድ በበኩላቸው አምራቹንና ሸማቹን በቀጥታ የሚያገናኙ ሦስት ከሰንበት እስከ ሰንበት የግብይት ማዕከላት መቋቋማቸውን ገልጸዋል።

በማዕከላቱ አማካኝነት ለማህበረሰቡ ምርት በቀጥታ እየቀረበ መሆኑን ገልጸው፣ ይህም ማህበረሰቡ በአቅሙ የሚፈልገውን እንዲሸምት ዕድል ፈጥሯል ብለዋል።
በቀጣይም ተጨማሪ ማዕከላትን በማስፋፋት ህብረተሰቡን ይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግ እንደሚሰራ ገልፀዋል።
ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ የተገኘው መረጃ እንደሚያሳየው አምራቹንና ነጋዴውን በቀጥታ የሚያገናኙ 134 ከሰንበት እስከ ሰንበት የግብይት ማዕከላት በክልሉ ተቋቁመው አገልግሎት በመስጠት ላይ ናቸው።
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026