የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>ከእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶች ወጪ ንግድ ከ63 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል</p>

Mar 5, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 26/2017(ኢዜአ)፡-በተያዘው በጀት ዓመት ሰባት ወራት ከእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶች ወጪ ንግድ ከ63 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት አስታወቀ።

የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ሳህሉ ሙሉ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ኢንስቲትየቱ በበጀት ዓመቱ ከእንስሳት ምርትና ተዋጽኦ ማቀነባበርና ወጪ ንግድ 124 ሚሊየን ዶላር ገቢ ለማግኘት በርካታ ስራዎችን በማከናወን ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

እቅዱን ለማሳካት ጥራቱን የጠበቀ የእንስሳት ተዋጽኦ ምርት ለአለም ገበያ ማቅረብ የሚያስችል አቅም መፍጠር ይፈልጋል ብለዋል።

በዚህም ኢንስቲትዩቱ የተለያዩ የእንስሳት ምርቶችን ናሙና በመውሰድ የመፈተሽ እና በዘርፉ ላይ ተሰማርተው ለሚገኙ ኢንዱስትሪዎች ሙያዊ ድጋፍና ክትትል እያደረገ እንደሚገኝ ነው የተናገሩት።

በባለፉት ሰባት ወራት 12ሺህ 500 ሜትሪክ ቶን የተለያዩ የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶችን ለውጪ ገበያ ተደራሽ ማድረግ ተችሏል ብለዋል።

በዚህም ተቀነባብረው ለውጭ ገበያ ከቀረቡ ልዩ ልዩ የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶች ከ63 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘት መቻሉን ተናግረዋል።

ስጋ እና የስጋ ተረፈ ምርቶች በስፋት ከተላከባቸው የገልፍ ሀገራት መካከል የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ 45 በመቶውን የሚሸፍን ሲሆን ወደ ሳውዲ አረቢያም ተቀራራቢ የሆነ የምርት መጠን መላክ መቻሉን አክለዋል።

የስጋ ምርት መዳረሻ ሀገራትን ለማስፋት በአለም አቀፍ የገበያ መድረኮች ላይ የማስተዋወቅና የሚያስፈልጉ መስፈርቶችን የማሟላት አቅም የሚፈጥር ተግባራት በመከናወን ላይ ናቸው ብለዋል።

ከዚህም በተጨማሪ ኢንስቲትዩቱ የእንስሳት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የእንስሳት ዝርያ ማሻሻል ስራ በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህም 1 ነጥብ 92 ሚሊየን የዳልጋ ከብቶችን በሰው ሰራሽ ዘዴ በማዳቀል ዝርያቸው የተሻሻሉ ጥጆችን ማግኘት የሚያስችል ስራ መሰራቱን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026