
አዲስ አበባ፤ የካቲት 26/2017(ኢዜአ)፡-በተያዘው በጀት ዓመት ሰባት ወራት ከእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶች ወጪ ንግድ ከ63 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት አስታወቀ።
የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ሳህሉ ሙሉ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ኢንስቲትየቱ በበጀት ዓመቱ ከእንስሳት ምርትና ተዋጽኦ ማቀነባበርና ወጪ ንግድ 124 ሚሊየን ዶላር ገቢ ለማግኘት በርካታ ስራዎችን በማከናወን ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
እቅዱን ለማሳካት ጥራቱን የጠበቀ የእንስሳት ተዋጽኦ ምርት ለአለም ገበያ ማቅረብ የሚያስችል አቅም መፍጠር ይፈልጋል ብለዋል።
በዚህም ኢንስቲትዩቱ የተለያዩ የእንስሳት ምርቶችን ናሙና በመውሰድ የመፈተሽ እና በዘርፉ ላይ ተሰማርተው ለሚገኙ ኢንዱስትሪዎች ሙያዊ ድጋፍና ክትትል እያደረገ እንደሚገኝ ነው የተናገሩት።
በባለፉት ሰባት ወራት 12ሺህ 500 ሜትሪክ ቶን የተለያዩ የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶችን ለውጪ ገበያ ተደራሽ ማድረግ ተችሏል ብለዋል።
በዚህም ተቀነባብረው ለውጭ ገበያ ከቀረቡ ልዩ ልዩ የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶች ከ63 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘት መቻሉን ተናግረዋል።
ስጋ እና የስጋ ተረፈ ምርቶች በስፋት ከተላከባቸው የገልፍ ሀገራት መካከል የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ 45 በመቶውን የሚሸፍን ሲሆን ወደ ሳውዲ አረቢያም ተቀራራቢ የሆነ የምርት መጠን መላክ መቻሉን አክለዋል።
የስጋ ምርት መዳረሻ ሀገራትን ለማስፋት በአለም አቀፍ የገበያ መድረኮች ላይ የማስተዋወቅና የሚያስፈልጉ መስፈርቶችን የማሟላት አቅም የሚፈጥር ተግባራት በመከናወን ላይ ናቸው ብለዋል።
ከዚህም በተጨማሪ ኢንስቲትዩቱ የእንስሳት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የእንስሳት ዝርያ ማሻሻል ስራ በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም 1 ነጥብ 92 ሚሊየን የዳልጋ ከብቶችን በሰው ሰራሽ ዘዴ በማዳቀል ዝርያቸው የተሻሻሉ ጥጆችን ማግኘት የሚያስችል ስራ መሰራቱን ተናግረዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026