
አዲስ አበባ፤ የካቲት 26/2017(ኢዜአ)፡-በተያዘው በጀት ዓመት ሰባት ወራት ከእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶች ወጪ ንግድ ከ63 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት አስታወቀ።
የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ሳህሉ ሙሉ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ኢንስቲትየቱ በበጀት ዓመቱ ከእንስሳት ምርትና ተዋጽኦ ማቀነባበርና ወጪ ንግድ 124 ሚሊየን ዶላር ገቢ ለማግኘት በርካታ ስራዎችን በማከናወን ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
እቅዱን ለማሳካት ጥራቱን የጠበቀ የእንስሳት ተዋጽኦ ምርት ለአለም ገበያ ማቅረብ የሚያስችል አቅም መፍጠር ይፈልጋል ብለዋል።
በዚህም ኢንስቲትዩቱ የተለያዩ የእንስሳት ምርቶችን ናሙና በመውሰድ የመፈተሽ እና በዘርፉ ላይ ተሰማርተው ለሚገኙ ኢንዱስትሪዎች ሙያዊ ድጋፍና ክትትል እያደረገ እንደሚገኝ ነው የተናገሩት።
በባለፉት ሰባት ወራት 12ሺህ 500 ሜትሪክ ቶን የተለያዩ የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶችን ለውጪ ገበያ ተደራሽ ማድረግ ተችሏል ብለዋል።
በዚህም ተቀነባብረው ለውጭ ገበያ ከቀረቡ ልዩ ልዩ የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶች ከ63 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘት መቻሉን ተናግረዋል።
ስጋ እና የስጋ ተረፈ ምርቶች በስፋት ከተላከባቸው የገልፍ ሀገራት መካከል የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ 45 በመቶውን የሚሸፍን ሲሆን ወደ ሳውዲ አረቢያም ተቀራራቢ የሆነ የምርት መጠን መላክ መቻሉን አክለዋል።
የስጋ ምርት መዳረሻ ሀገራትን ለማስፋት በአለም አቀፍ የገበያ መድረኮች ላይ የማስተዋወቅና የሚያስፈልጉ መስፈርቶችን የማሟላት አቅም የሚፈጥር ተግባራት በመከናወን ላይ ናቸው ብለዋል።
ከዚህም በተጨማሪ ኢንስቲትዩቱ የእንስሳት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የእንስሳት ዝርያ ማሻሻል ስራ በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም 1 ነጥብ 92 ሚሊየን የዳልጋ ከብቶችን በሰው ሰራሽ ዘዴ በማዳቀል ዝርያቸው የተሻሻሉ ጥጆችን ማግኘት የሚያስችል ስራ መሰራቱን ተናግረዋል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026