የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የሕዝቡን ዘላቂ ጥቅም የሚያረጋግጡ የልማት ሥራዎች በስፋት እየተከናወኑ ነው - አቶ አደም ፋራህ

Mar 10, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 29/2017(ኢዜአ)፦ የሕዝቡን ዘላቂ ጥቅም የሚያረጋግጡ የልማት ሥራዎች በስፋት እየተከናወኑ እንደሚገኝ የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ ገለጹ።


አቶ አደም ፋራህ የብልጽግና ፓርቲ እሳቤዎች መሰረት በማድረግ በመላው ኢትዮጵያ የህዝብን ጥቅም በዘላቂነት ለማረጋገጥ እየተሰራ እንደሚገኝ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል።


ከእነዚህ የልማት ስራዎች መካከል በአማራ ክልል በደቡብ ወሎ ዞን መንደርንና ቤተሰብን ማዕከል በማድረግ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር እንደሚገኝበት ለአብነት ጠቅሰዋል።


መርሃ ግብሩን ከወጣቶች ስራ ዕድል ፈጠራ ጋር በማስተሳሰር ውጤታማ ስራዎች ማከናወን መቻሉንም አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.