የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የስራ ዕድል ፈጠራ አማራጮችን በማስፋት የሴቶችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተሰራ ነው

Mar 10, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 29/2017(ኢዜአ)፡- የስራ ዕድል ፈጠራ አማራጮችን በማስፋት የሴቶችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን የአዲስ አበባ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ አስታወቀ።

አለምአቀፉን የሴቶች ቀንን ምክንያት በማድረግ በሴቶች የተመረቱ ምርቶች ባዛርና ኤግዚቢሽን፣ የምርት ማሳያ ጋለሪዎች እንዲሁም የነገዋ የሴቶች ተሀድሶና ክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከል ላይ ጉብኝት ተደርጓል።


ጉብኝቱን ያደረጉት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ፣ የአዲስ አበባ ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ሃላፊ ወይንሸት ዘሪሁንን፣ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች እንዲሁም የተለያዩ አገራት ሴት አምባሳደሮች ናቸው።

የአዲስ አበባ ሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወይንሸት ዘሪሁን መንግስት ባለፉት ዓመታት የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳታፊነትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተለያዩ ተግባራትን አከናውኗል።

በዚህም ሴቶች ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተሳትፎ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጎለበተ መጥቷል ነው ያሉት።


ቢሮው የተለያዩ የስራ ዕድል ፈጠራ አማራጮችን በማስፋት የሴቶችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ መሆኑንም አንስተዋል።

በሴቶች ብቻ የተመረቱ የተለያዩ ምርቶችም የዚሁ ማሳያ መሆናቸውን በመጥቀስ።

ቢሮው በቀጣይም የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራዊ እርምጃዎችን እንደሚወስድ አረጋግጠዋል።

ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ''ፈጣንና ቀጣይነት ያለው ሁሉን አቀፍ ለውጥ በሴቶች ተሳትፎ ይረጋገጣል'' በሚል መሪ ሀሳብ በዓለም ደረጃ ለ114ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ49ኛ ጊዜ እየተከበረ ይገኛል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026