
አዲስ አበባ፤ የካቲት 29/2017(ኢዜአ)፡- የስራ ዕድል ፈጠራ አማራጮችን በማስፋት የሴቶችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን የአዲስ አበባ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ አስታወቀ።
አለምአቀፉን የሴቶች ቀንን ምክንያት በማድረግ በሴቶች የተመረቱ ምርቶች ባዛርና ኤግዚቢሽን፣ የምርት ማሳያ ጋለሪዎች እንዲሁም የነገዋ የሴቶች ተሀድሶና ክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከል ላይ ጉብኝት ተደርጓል።

ጉብኝቱን ያደረጉት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ፣ የአዲስ አበባ ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ሃላፊ ወይንሸት ዘሪሁንን፣ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች እንዲሁም የተለያዩ አገራት ሴት አምባሳደሮች ናቸው።
የአዲስ አበባ ሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወይንሸት ዘሪሁን መንግስት ባለፉት ዓመታት የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳታፊነትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተለያዩ ተግባራትን አከናውኗል።
በዚህም ሴቶች ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተሳትፎ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጎለበተ መጥቷል ነው ያሉት።

ቢሮው የተለያዩ የስራ ዕድል ፈጠራ አማራጮችን በማስፋት የሴቶችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ መሆኑንም አንስተዋል።
በሴቶች ብቻ የተመረቱ የተለያዩ ምርቶችም የዚሁ ማሳያ መሆናቸውን በመጥቀስ።
ቢሮው በቀጣይም የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራዊ እርምጃዎችን እንደሚወስድ አረጋግጠዋል።
ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ''ፈጣንና ቀጣይነት ያለው ሁሉን አቀፍ ለውጥ በሴቶች ተሳትፎ ይረጋገጣል'' በሚል መሪ ሀሳብ በዓለም ደረጃ ለ114ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ49ኛ ጊዜ እየተከበረ ይገኛል።
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026