የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በክልሉ ባለፉት ሰባት ወራት በመንገድ ጥገናና ግንባታ የተሻለ አፈጻጸም ተመዝግቧል - ቢሮው

Mar 10, 2025

IDOPRESS

ደሴ የካቲት 30/2017 (ኢዜአ)- በአማራ ክልል ባለፉት ሰባት ወራት 8 ሺህ 929 ኪሎ ሜትር የነባር መንገድ ጥገናና የአዲስ መንገድ ግንባታ ማከናወን መቻሉን የክልሉ መንገድ ቢሮ አስታወቀ ።ፎቶ አለው


ቢሮው የ2017 ዓ.ም የሰባት ወራት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ በደሴ ከተማ እያካሄደ ነው።


የቢሮው ኃላፊው ጋሻው አወቀ(ዶ/ር) በመድረኩ እንደገለፁት በክልሉ ነባር መንገዶችን በመጠገንና አዳዲስ መንገዶችን በመገንባት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የማድረግ ሥራ እየተከናወነ ነው።


ይህም የመንገድ ተደራሽነትን በማስፋት የክልሉን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገት በማሳለጥ እንዲሁም የህብረተሰቡን መስተጋብር ለማፋጠን የሚያስችል ስራ መሰራቱን አስረድተዋል።


በበጀት ዓመቱ ሰባት ወራት ከተከናወነው 8 ሺህ 929 ኪሎ ሜትር ውስጥም 8 ሺህ 600 ኪሎ ሜትር የሚሆነው የነባር መንገዶች ጥገና ሲሆን፤ ቀሪው 329 ኪሎ ሜትር ደግሞ የአዲስ መንገድ ግንባታ ነው ብለዋል።

በአዲስ የመንገድ ግንባታና በነባር መንገዶች ጥገና ስራው ላይም ህብረተሰቡ በገንዘብ፣ በጉልበቱና በቁሳቁስ እያደረገ ያለው ድጋፍ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ ምመጣቱን ተናግረዋል።


ይህም ቢሮው ክረምቱ ከመግባቱ በፊት በቀሪ ወራት በሁሉም ዘርፎች የታሻለ አፈጻጸም ለማስመዝገብ የያዘውን ግብ ለማሳካት እንደሚያስችል ያላቸውን እምነት አስገንዝበዋል።


በደቡብ ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን በበኩላቸው በዞኑ የመንገድ ተደራሽነቱን በማሳደግና በአገልግሎት ብዛት የተበላሹትን በመጠገን ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል።


በዚህም ባለፉት ወራት አበረታች ውጤት ማስመዝገብ የተቻለ ቢሆንም ከህብረተሰቡ የመልማት ፍላጎት አንጻር ሲታይ በቀጣይ ወራት የጋራ ርብርብ የሚጠይቅ ነው ብለዋል።


በመድረኩ የክልል፣ የዞን፣ የከተማ አመራር አባላትን ጨምሮ አጋርና ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.