
ደሴ የካቲት 30/2017 (ኢዜአ)- በአማራ ክልል ባለፉት ሰባት ወራት 8 ሺህ 929 ኪሎ ሜትር የነባር መንገድ ጥገናና የአዲስ መንገድ ግንባታ ማከናወን መቻሉን የክልሉ መንገድ ቢሮ አስታወቀ ።ፎቶ አለው
ቢሮው የ2017 ዓ.ም የሰባት ወራት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ በደሴ ከተማ እያካሄደ ነው።
የቢሮው ኃላፊው ጋሻው አወቀ(ዶ/ር) በመድረኩ እንደገለፁት በክልሉ ነባር መንገዶችን በመጠገንና አዳዲስ መንገዶችን በመገንባት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የማድረግ ሥራ እየተከናወነ ነው።
ይህም የመንገድ ተደራሽነትን በማስፋት የክልሉን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገት በማሳለጥ እንዲሁም የህብረተሰቡን መስተጋብር ለማፋጠን የሚያስችል ስራ መሰራቱን አስረድተዋል።
በበጀት ዓመቱ ሰባት ወራት ከተከናወነው 8 ሺህ 929 ኪሎ ሜትር ውስጥም 8 ሺህ 600 ኪሎ ሜትር የሚሆነው የነባር መንገዶች ጥገና ሲሆን፤ ቀሪው 329 ኪሎ ሜትር ደግሞ የአዲስ መንገድ ግንባታ ነው ብለዋል።
በአዲስ የመንገድ ግንባታና በነባር መንገዶች ጥገና ስራው ላይም ህብረተሰቡ በገንዘብ፣ በጉልበቱና በቁሳቁስ እያደረገ ያለው ድጋፍ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ ምመጣቱን ተናግረዋል።
ይህም ቢሮው ክረምቱ ከመግባቱ በፊት በቀሪ ወራት በሁሉም ዘርፎች የታሻለ አፈጻጸም ለማስመዝገብ የያዘውን ግብ ለማሳካት እንደሚያስችል ያላቸውን እምነት አስገንዝበዋል።
በደቡብ ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን በበኩላቸው በዞኑ የመንገድ ተደራሽነቱን በማሳደግና በአገልግሎት ብዛት የተበላሹትን በመጠገን ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል።

በዚህም ባለፉት ወራት አበረታች ውጤት ማስመዝገብ የተቻለ ቢሆንም ከህብረተሰቡ የመልማት ፍላጎት አንጻር ሲታይ በቀጣይ ወራት የጋራ ርብርብ የሚጠይቅ ነው ብለዋል።
በመድረኩ የክልል፣ የዞን፣ የከተማ አመራር አባላትን ጨምሮ አጋርና ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው።
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026