
ደሴ የካቲት 30/2017 (ኢዜአ)- በአማራ ክልል ባለፉት ሰባት ወራት 8 ሺህ 929 ኪሎ ሜትር የነባር መንገድ ጥገናና የአዲስ መንገድ ግንባታ ማከናወን መቻሉን የክልሉ መንገድ ቢሮ አስታወቀ ።ፎቶ አለው
ቢሮው የ2017 ዓ.ም የሰባት ወራት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ በደሴ ከተማ እያካሄደ ነው።
የቢሮው ኃላፊው ጋሻው አወቀ(ዶ/ር) በመድረኩ እንደገለፁት በክልሉ ነባር መንገዶችን በመጠገንና አዳዲስ መንገዶችን በመገንባት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የማድረግ ሥራ እየተከናወነ ነው።
ይህም የመንገድ ተደራሽነትን በማስፋት የክልሉን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገት በማሳለጥ እንዲሁም የህብረተሰቡን መስተጋብር ለማፋጠን የሚያስችል ስራ መሰራቱን አስረድተዋል።
በበጀት ዓመቱ ሰባት ወራት ከተከናወነው 8 ሺህ 929 ኪሎ ሜትር ውስጥም 8 ሺህ 600 ኪሎ ሜትር የሚሆነው የነባር መንገዶች ጥገና ሲሆን፤ ቀሪው 329 ኪሎ ሜትር ደግሞ የአዲስ መንገድ ግንባታ ነው ብለዋል።
በአዲስ የመንገድ ግንባታና በነባር መንገዶች ጥገና ስራው ላይም ህብረተሰቡ በገንዘብ፣ በጉልበቱና በቁሳቁስ እያደረገ ያለው ድጋፍ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ ምመጣቱን ተናግረዋል።
ይህም ቢሮው ክረምቱ ከመግባቱ በፊት በቀሪ ወራት በሁሉም ዘርፎች የታሻለ አፈጻጸም ለማስመዝገብ የያዘውን ግብ ለማሳካት እንደሚያስችል ያላቸውን እምነት አስገንዝበዋል።
በደቡብ ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን በበኩላቸው በዞኑ የመንገድ ተደራሽነቱን በማሳደግና በአገልግሎት ብዛት የተበላሹትን በመጠገን ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል።

በዚህም ባለፉት ወራት አበረታች ውጤት ማስመዝገብ የተቻለ ቢሆንም ከህብረተሰቡ የመልማት ፍላጎት አንጻር ሲታይ በቀጣይ ወራት የጋራ ርብርብ የሚጠይቅ ነው ብለዋል።
በመድረኩ የክልል፣ የዞን፣ የከተማ አመራር አባላትን ጨምሮ አጋርና ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026