
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 2/2017(ኢዜአ)፦ ከ78 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር በላይ ካፒታል የተመደበለት ባለ ብዙ ዘርፍ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ግንባታ እንዲከናወን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ቦርድ ውሳኔ አሳለፈ።
ቦርዱ ባካሄደው ስብሰባ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን ያሳለፈ ሲሆን ከውሳኔዎቹ መካከል በአንድ ባለሀብት ባለ ብዙ ዘርፍ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ለመገንባት የቀረበው ጥያቄ በፍጥነት ወደ ሥራ እንዲገባ ያሳለፈው ውዳኔ ይገኝበታል።

በጥያቄው ላይ ቦርዱ በስፋት ከተወያየ በኋላ ባለ ብዙ ዘርፍ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ሆኖ እንዲሰየም እና ጥያቄ አቅራቢዎቹም በፍጥነት ወደ ሥራ እንዲገቡ ውሳኔ ማሳለፉን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን መረጃ ያመላክታል።
በተጨማሪም የልዩ ኢኮኖሚ ዞን አሰያየም፣ የመሬት አመዳደብ እና አጠቃቀም መመርያን ጨምሮ በቀረቡለት ሌሎች ጉዳዮች ላይ በመወያየት ውሳኔ መስጠቱም ተመላክቷል።
ቦርዱ በሀገሪቱ ምቹ እና ሳቢ የኢንቨስትመንት ከባቢ ለመፍጠር ያለውን ቁርጠኝነት እእነዲሁም ለኮሚሽኑ የሚሰጠውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል መግለጹም በመረጃው ተጠቅሷል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026