አዲስ አበባ፤ መጋቢት 2/2017(ኢዜአ)፦ ከ78 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር በላይ ካፒታል የተመደበለት ባለ ብዙ ዘርፍ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ግንባታ እንዲከናወን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ቦርድ ውሳኔ አሳለፈ።
ቦርዱ ባካሄደው ስብሰባ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን ያሳለፈ ሲሆን ከውሳኔዎቹ መካከል በአንድ ባለሀብት ባለ ብዙ ዘርፍ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ለመገንባት የቀረበው ጥያቄ በፍጥነት ወደ ሥራ እንዲገባ ያሳለፈው ውዳኔ ይገኝበታል።
በጥያቄው ላይ ቦርዱ በስፋት ከተወያየ በኋላ ባለ ብዙ ዘርፍ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ሆኖ እንዲሰየም እና ጥያቄ አቅራቢዎቹም በፍጥነት ወደ ሥራ እንዲገቡ ውሳኔ ማሳለፉን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን መረጃ ያመላክታል።
በተጨማሪም የልዩ ኢኮኖሚ ዞን አሰያየም፣ የመሬት አመዳደብ እና አጠቃቀም መመርያን ጨምሮ በቀረቡለት ሌሎች ጉዳዮች ላይ በመወያየት ውሳኔ መስጠቱም ተመላክቷል።
ቦርዱ በሀገሪቱ ምቹ እና ሳቢ የኢንቨስትመንት ከባቢ ለመፍጠር ያለውን ቁርጠኝነት እእነዲሁም ለኮሚሽኑ የሚሰጠውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል መግለጹም በመረጃው ተጠቅሷል።
አዲስ አበባ ፤የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርት ተገልጋዮች ፋይዳ መታወቂያን ተጠቅመው በዲጂታል አማራጭ ትኬት የሚቆርጡበት አሰራር ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 03/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የለማ የትራንስፖርት ኦፕሬተሮችንና የጭነት ባለቤቶችን የሚገናኝ መተግበሪያ አስጀምሯል። ...
Feb 12, 2025