
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 2/2017(ኢዜአ)፦ ከ78 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር በላይ ካፒታል የተመደበለት ባለ ብዙ ዘርፍ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ግንባታ እንዲከናወን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ቦርድ ውሳኔ አሳለፈ።
ቦርዱ ባካሄደው ስብሰባ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን ያሳለፈ ሲሆን ከውሳኔዎቹ መካከል በአንድ ባለሀብት ባለ ብዙ ዘርፍ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ለመገንባት የቀረበው ጥያቄ በፍጥነት ወደ ሥራ እንዲገባ ያሳለፈው ውዳኔ ይገኝበታል።

በጥያቄው ላይ ቦርዱ በስፋት ከተወያየ በኋላ ባለ ብዙ ዘርፍ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ሆኖ እንዲሰየም እና ጥያቄ አቅራቢዎቹም በፍጥነት ወደ ሥራ እንዲገቡ ውሳኔ ማሳለፉን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን መረጃ ያመላክታል።
በተጨማሪም የልዩ ኢኮኖሚ ዞን አሰያየም፣ የመሬት አመዳደብ እና አጠቃቀም መመርያን ጨምሮ በቀረቡለት ሌሎች ጉዳዮች ላይ በመወያየት ውሳኔ መስጠቱም ተመላክቷል።
ቦርዱ በሀገሪቱ ምቹ እና ሳቢ የኢንቨስትመንት ከባቢ ለመፍጠር ያለውን ቁርጠኝነት እእነዲሁም ለኮሚሽኑ የሚሰጠውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል መግለጹም በመረጃው ተጠቅሷል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026