ባሕር ዳር፤ መጋቢት 3/2017(ኢዜአ)፡- በባሕር ዳር የከተማ ግብርና ከ4 ሺህ 800 ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ እየለማ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ የግብሮና መምሪያ አስታወቀ።
በመምሪያው የሆልቲካልቸር ባለሙያ ሞላልኝ መንግስቱ፤ በአስተዳደሩ የከተማ ግብርናን በማስፋፋት በምግብ ራስን ለመቻል የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም አሁን ላይ 4 ሺህ 893 ሄክታር መሬት በበጋ መስኖ እየለማ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከዚህም 299 ሺህ ኩንታል ምርት ይጠበቃል ብለዋል።
ከዚህም 3 ሺህ 200 ሄክታር የሚሆነው በስንዴ ሰብል የተሸፈነ መሆኑን ጠቁመው፤ ከ136 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት የሚጠበቅ መሆኑን ገልጸዋል።
በከተማ የግብርና ልማት በምግብ ራስን ለመቻልና የተሻለ አመጋገብ እንዲኖር ከማድረግ ባለፈ ለበርካቶች የስራ እድል የፈጠረ መሆኑን ነው ባለሙያው ያስረዱት።
በዘርፉ ልማት ከተሰማሩ ወጣቶች መካከል ልሳነወርቅ ሰይፉ በሰጠው አስተያየት፤ በርካታ ወጣቶች በከተማ ግብርና የስራ እድል ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግሯል።
በማህበር ተደራጅተው ከሚያከናውኑት የአትክልት ልማት በተያዘው ዓመት እስከ 100 ሺህ ብር ለማግኘት አቅደዋል።
በማህበሩ በቋሚነት ተቀጥሮ የሚሰራው ወጣት ግዛት ክፍሌ፤ በዘርፉ ልማት ለበርካቶቻችን የስራ እድል ተፈጥሮልን ተጠቃሚ ሆነናል ብሏል።
ከዚህ በሚያገኘው ገቢ በመቆጠብ በቀጣይ የራሱን ቋሚ ስራ ለመጀመር እቅድ ያለው መሆኑንም ተናግሯል።
በከተማ አስተዳደሩ ባለፈው ዓመት ከተካሄደው የበጋ መስኖ ልማት ከ230 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱ ታውቋል።
አዲስ አበባ ፤የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርት ተገልጋዮች ፋይዳ መታወቂያን ተጠቅመው በዲጂታል አማራጭ ትኬት የሚቆርጡበት አሰራር ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 03/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የለማ የትራንስፖርት ኦፕሬተሮችንና የጭነት ባለቤቶችን የሚገናኝ መተግበሪያ አስጀምሯል። ...
Feb 12, 2025