የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በከተማዋ ከ4 ሺህ 800 ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ እየለማ ነው

Mar 13, 2025

IDOPRESS

ባሕር ዳር፤ መጋቢት 3/2017(ኢዜአ)፡- በባሕር ዳር የከተማ ግብርና ከ4 ሺህ 800 ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ እየለማ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ የግብሮና መምሪያ አስታወቀ።



በመምሪያው የሆልቲካልቸር ባለሙያ ሞላልኝ መንግስቱ፤ በአስተዳደሩ የከተማ ግብርናን በማስፋፋት በምግብ ራስን ለመቻል የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህም አሁን ላይ 4 ሺህ 893 ሄክታር መሬት በበጋ መስኖ እየለማ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከዚህም 299 ሺህ ኩንታል ምርት ይጠበቃል ብለዋል።

ከዚህም 3 ሺህ 200 ሄክታር የሚሆነው በስንዴ ሰብል የተሸፈነ መሆኑን ጠቁመው፤ ከ136 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት የሚጠበቅ መሆኑን ገልጸዋል።

በከተማ የግብርና ልማት በምግብ ራስን ለመቻልና የተሻለ አመጋገብ እንዲኖር ከማድረግ ባለፈ ለበርካቶች የስራ እድል የፈጠረ መሆኑን ነው ባለሙያው ያስረዱት።


በዘርፉ ልማት ከተሰማሩ ወጣቶች መካከል ልሳነወርቅ ሰይፉ በሰጠው አስተያየት፤ በርካታ ወጣቶች በከተማ ግብርና የስራ እድል ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግሯል።

በማህበር ተደራጅተው ከሚያከናውኑት የአትክልት ልማት በተያዘው ዓመት እስከ 100 ሺህ ብር ለማግኘት አቅደዋል።


በማህበሩ በቋሚነት ተቀጥሮ የሚሰራው ወጣት ግዛት ክፍሌ፤ በዘርፉ ልማት ለበርካቶቻችን የስራ እድል ተፈጥሮልን ተጠቃሚ ሆነናል ብሏል።

ከዚህ በሚያገኘው ገቢ በመቆጠብ በቀጣይ የራሱን ቋሚ ስራ ለመጀመር እቅድ ያለው መሆኑንም ተናግሯል።

በከተማ አስተዳደሩ ባለፈው ዓመት ከተካሄደው የበጋ መስኖ ልማት ከ230 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱ ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026