የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ኮሚቴው በጅቡቲ ያለውን የአፈር ማዳበሪያ የጭነት ሂደት ጎበኘ

Mar 15, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 5/2017(ኢዜአ)፦ የጂቡቲ የማዳበሪያ ኦፕሬሽን ኮሚቴ በአሮጌ ወደብ ከጂቡቲ ወደ ኢትዮጵያ በመጓጓዝ ላይ ያለውን የአፈር ማዳበሪያ ጭነት እንቅስቃሴ ተመልክቷል።


ኮሚቴው በቀን በአማካይ እስከ 7000 ሜትሪክ ቶን የዩሪያ ማዳበሪያ የሚጫንበት እና ከ112 በላይ ከባድ ተሽከርካሪዎች ማዳበሪያውን ጭነው ከተርሚናሉ ወደ ኢትዮጵያ የሚጓዙበትን ሂደት ላይ ምልከታ አድርጓል።


የአፈር ማዳበሪያውን የማጓጓዝ ሂደቱ ዘላቂነት ባለው እንዲቀጥል እየተደረገ ያለው ጥረት አበረታች መሆኑን በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.