የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የግዥ ስርዓት ችግርና የፕሮጀክቶች አፈፃፀም መጓተት አፋጣኝ መፍትሔ የሚሹ ናቸው - ኮሚሽኑ

Mar 17, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ ፤መጋቢት 6/2017(ኢዜአ)፦በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚስተዋሉ የግዥ ስርዓትና የፕሮጀክቶች አፈፃፀም መጓተት አፋጣኝ መፍትሔ የሚሹ መሆናቸውን የፌዴራል የሥነ-ምግባርና የጸረ-ሙስና ኮሚሽን ገለጸ።

የትምህርት ሚኒስቴር በበኩሉ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለሙስና እና ብልሹ አሰራር ተጋላጭ የሚያደርጉ ችግሮችን ለመቅረፍ በቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራር ለመዘርጋት እየሰራ መሆኑን አመላክቷል።


የፌዴራል የሥነ-ምግባርና የጸረ-ሙስና ኮሚሽን በትምህርት ዘርፍ የሙስና ሥጋት ተጋላጭነት ዙሪያ ባደረገው ጥናት ላይ ከተጠሪ ተቋማትና ባለድርሻ አካላት ጋር ተወያይቷል።

የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር እሸቴ አስፋው የግዥ፣ የፕሮጀክቶች አፈፃፀም መዘግየት፣ የመምህራን በተደጋጋሚ በክፍል አለመገኘትና ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃ ጉዳዮች ላይ የሙስና ተጋላጭነት መኖሩ በጥናቱ መለየቱን ገልጸዋል።

ህገወጥ ቅጥር፣ ዝውውርና የደረጃ እድገት፣ የክትትልና የድጋፍ ስርዓት አለመገንባትን ጨምሮ የአሰራር ግልፅነት መጓደል መኖሩን የጥናቱ ግኝት ያሳያል ብለዋል።

የጥናት ግኝቱ በሶስት ደረጃዎች መለየቱን ተናግረው በዚሁ መሰረት ለችግሩ ከአፋጣኝ ጀምሮ ዘላቂ መፍትሄ ማበጀት እንደሚገባም ገልጸዋል።

በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሽኔ፤ በዘርፉ የተለዩ የሙስና ተጋላጭነት እና ለብልሹ አሰራር የሚዳርጉ ችግሮችን ለመቅረፍ በቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራር ይዘረጋል ብለዋል።

ከዚህም ባሻገር ተጠያቂነትን የማረጋገጥና የሙስና መከላከል አቅምን የማሳደግ ስራ በስፋት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።

በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አየለች እሸቴ በበኩላቸው በጥናት ለተለዩ ስጋቶች የሚመለከታቸው ተቋማት ዘላቂ የመፍትሔ እርምጃ እንደሚወስዱ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026