
ሀዋሳ፤ መጋቢት 6/2017 (ኢዜአ)--የጤና ጉዳት የሚያስከትል አዮዲን ያልተቀላቀለበት የገበታ ጨው በህገወጥ መንገድ ሲመረት ተገኝቶ መያዙን የኢትዮጵያ ምግብና መድሀኒት ባለስልጣን ሀዋሳ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
ምርቱ የተያዘው ባለስልጣኑ ከሲዳማ ክልል ጤናና ጤናነክ ግብዓት ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣንና ከተለያዩ የጸጥታ አካላት ጋር ተቀናጅቶ ባደረገው ክትትል መሆኑም ተገልጿል።
የኢትዮጵያ ምግብና መድሀኒት ባለስልጣን ሀዋሳ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ፍቃዱ ንማኔ እንደገለጹት፣ ጽህፈት ቤቱ በሲዳማ፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልሎችና በኦሮሚያ ክልል ስምንት ዞኖችና አምስት የከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም በሶማሌ ክልል ሊበንና ዳዋ ዞኖች የክትትልና ቁጥጥር ስራ ያከናውናል።
በእነዚህ አካባቢዎች ባለፉት ሁለት ወራት በ1ሺህ 800 ተቋማት ላይ የቁጥጥር ሥራዎች ማከናወኑን ጠቅሰው፣ በዚህም ጊዜ ያለፈባቸው፣ መስፈርት የማያሟሉ፣ ያለፈቃድ በመኖሪያ ቤት ጭምር የተመረቱ 42 አይነት የጨውና የተለያዩ ምርቶች ተገኝተው ከገበያ እንዲሰበሰቡ መደረጉን ገልጸዋል።
የጨው ማምረቻ ስፍራና የአመራረት ሂደቱ የንጽህና ችግር ያለበት ከመሆኑ ባለፈ ለቆዳ ፋብሪካ ግብዓትነት የሚውል ጨው በመፍጨት "አይኦዲን አለው" በሚል ታሽጎ ለገበያ ሲቀርብ እንደነበረም ሃላፊው ተናግረዋል።
በቅንጅት በተደረገ ክትትል በለኩና በሃዋሳ ከተሞች ለጤና ጠንቅ የሆነና አዮዲን የሌለው ጨው በግለሰብ ቤት ሲመረት ተገኝቶ መያዙንም ገልጸዋል።
በእዚህም በተለያየ መጠን ታሽጎ የተዘጋጀ ጨው፣ ያልተፈጨ ጥሬ ጨው፣ የማሸጊያ ማሽን፣ የጨው መፍጫ እና የተለያዩ ማሸጊያዎችም አብሮ መያዙን ተናግረዋል።
ህብረተሰቡ የጤና ጉዳት የሚያስከትሉ ደረጃቸውን ያልጠበቁ ምርቶችን ከመጠቀም እንዲቆጠብ አሳሰብው በማሳያነትም የተወሰኑትን የጨው ምርቶች ገልጸዋል።
የሲዳማ ክልል ጤናና ጤናነክ ግብዓት ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ቡረሶ ቡላሾ በበኩላቸው፣ ደረጃቸውን ያልጠበቁ የጨው ምርቶች ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመሩ መምጣታቸውን በተደረገ ክትትል መረጋገጡን ገልጸዋል።
ለአብነትም ባለፉት ሁለት ወራት በቅንጅት በተከናወኑ ሥራዎች በርካታ የጨው ምርቶችን መያዛቸውን ነው የተናገሩት።
በለኩ ከተማ በመኖሪያ ቤት ውስጥ የተለያዩ ማሸጊያዎችን በመጠቀም በድብቅ የታሸገ ጨው በማዘጋጀት ለገበያ ሲያቀርብ የነበረ ግለሰብም በቁጥጥር ስር ውሏል ብለዋል።
ምንም አዮዲን የሌለውንና ለቆዳ ፋብሪካ የሚውል ጨውን በማስመጣት ፈጭቶ ለገበያ ሲያቀርብ የነበረ ግለሰብ ለህግ በማቅረብ በእስር እንዲቀጣ መደረጉንም ተናግረዋል።
ህብረተሰቡ አጠራጣሪና የማይታወቁ ምርቶች በገበያ ሲያጋጥመው ለኢትዮጵያ ምግብና መድሀኒት ባለስልጣን ነጻ የስልክ መስመር 8482 ጥቆማ በመስጠት ትብብሩን እንዲያሳይም የሀዋሳ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ፍቃዱ አሳስበዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026